Superadmin
Thu, 07/09/2026 - 11:35
በ«የይቅርታ ተጠቃሚ የሕግ ታራሚዎች ምልመላና መረጣ ረቂቅ መመሪያ» ላይ አስተያየት ይስጡ!
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፍትህ ቢሮ በ2018 በጀት ዓመት እያዘጋጃቸው ከሚገኙ ረቂቅ መመሪያዎች መካከል አንዱ የ«የይቅርታ ተጠቃሚ የሕግ ታራሚዎች ምልመላና መረጣ ረቂቅ መመሪያ» ነው።
ቢሮው ረቂቅ መመሪያውን ይበልጥ የተሟላና ጥራት ያለው ለማድረግ በሚካሄዱ የውይይት መድረኮች ከሚሰበሰቡ ግብዓቶች በተጨማሪ፣ ከህብረተሰቡ የሚቀርቡ ገንቢ ሐሳቦችንና አስተያየቶችን በቢሮው ድረ ገጽ ፣ በቴሌግራም ገጽ እና በነፃ የጥሪ ማዕከል በ 8651 አማካኝነት ለመቀበል ይፈልጋል።
ስለሆነም በረቂቅ መመሪያው ላይ ያላችሁን ገንቢ ሐሳብና አስተያየት በተዘጋጁት መገናኛ አማራጮች እንድታደርሱን በአክብሮት እንጋብዛለን።
"የእርስዎ ገንቢ ሐሳብ የተሻለ የሕግ ሥርዓት ግንባታ አካል ነው!"
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፍትህ ቢሮ