የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የገቢ ግብር ማሻሻያ አዋጅን አጸደቀ
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የገቢ ግብር ማሻሻያ አዋጅን አጸደቀ
(ሆሳዕና፣ሐምሌ 10/2017)የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ የገቢ ግብር ማሻሻያ አዋጅን አፅድቋል።
አዋጁ ከመቀጠር የሚገኝ ገቢ ግብር ነፃ የተደረገውን የብር መጠን 600 ከነበረበት ወደ 2ሺህ ከፍ አድርጓል፤ 35 በመቶ የግብር ክፍያ መጠን መነሻው ከ14 ሺህ ብር በላይ በሆነ ደሞዝ ላይ ይተገበራል።
ከገቢ ግብር ነፃ የተደረገው 2ሺህ ብር አጠቃላይ ከሀገሪቱ ገቢ 38 ነጥብ 44 ቢልዮን ብር እንደሚያሳጣ ተገልጿል።
የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ደሳለኝ ወዳጆ ፤ ማሻሸያ አዋጁ የሀገሪቱን የገቢ መሰብሰብ አቅም ለማሳደግ የተቀመጠውን ግብ ታሳቢ በማድረግና ለልማት ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተዘጋጀ መሆኑን ገልፀዋል።
ክልሉን ከአፈር ማዳበሪያ እዳ ነፃ ለማድረግ የክልሉ መንግስት የወሰደው እርምጃ የሚደነቅ መሆኑን በኢፌዴሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ገለፀ።
ክልሉን ከአፈር ማዳበሪያ እዳ ነፃ ለማድረግ የክልሉ መንግስት የወሰደው እርምጃ የሚደነቅ መሆኑን በኢፌዴሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ገለፀ።
(ሆሳዕና ፣ሐምሌ 10/2017) ፣የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ እና የግብርና ሚኒስቴር በቅንጅት በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የ2017/18 ምርት ዘመን የግብርና ግብዓት አቅርቦት እና ስርጭት ላይ የተደረገ ሱፐርቪዥን ግብረ መልስ ለክልሉ ግብርና ቢሮ ሰጥቷል።
በኢፌዴሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርናና ገጠር ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢና የቡድኑ መሪ የተከበሩ ሰለሞን ላሌ ብልሹ አሰራርን በመታገል ክልሉን ከአፈር ማዳበሪያ እዳ ነፃ ለማድረግ የክልሉ መንግስት የወሰደው እርምጃ የሚደነቅ መሆኑን ተናግረዋል።
በክልሉ የአፈር ማዳበሪያ አቅርቦትና ምርጥ ዘር ስርጭት ላይ መሻሻሎች መኖሩን ተናግረው እርሶ አደሩ አማራጭ የተፈጥሮ ማዳበሪያ በስፋት እንዲጠቀም መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል።
መንግስት ለዘላቂ ሰላም እና ለሀገራዊ አንድነት በትኩረት እየሰራ ይገኛል-ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር)
መንግስት ለዘላቂ ሰላም እና ለሀገራዊ አንድነት በትኩረት እየሰራ ይገኛል-ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር)
ሆሳዕና ፤ሐምሌ 10/2017፦መንግስት ለዘላቂ ሰላም እና ለሀገራዊ አንድነት በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ እና ለዚህም አስተማማኝ መሰረት መጣሉን የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) ገለጹ።
የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) ለኢዜአ አመራሮች እና ሰራተኞች በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ እና ቀጣይ የስራ አቅጣጫ ሰጥተዋል።
ሚኒስትሩ በማብራሪያቸው፥ የተረጋጋ የፖለቲካ ስርዓት መሰረት የመጣል፣ገለልተኛ ተቋማትን የመገንባት እና ለሌብነት የማይመች የፖለቲካ ስርዓት መፍጠር ላይ ውጤታማ ስራዎች መከናወናቸውን አመልክተዋል።
ሚኒስትሩ አክለውም መንግስት ለዘላቂ ሰላም እና ለሀገራዊ አንድነት በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸው፥ ለዚህም አስተማማኝ መሰረት መጣሉን ተናግረዋል።
በክረምት ወራት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የሴቶችና ህፃናትን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትብብር መስራት እንደሚገባ ተመላከተ
በክረምት ወራት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የሴቶችና ህፃናትን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትብብር መስራት እንደሚገባ ተመላከተ
(ሆሳዕና፣ ሀምሌ 10/2017)፤ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ቢሮ እና የክልሉ የሴቶች አደረጃጀት የጋራ ፎረም የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ማስጀመሪያ መርሃ ግብር በማረቆ ልዩ ወረዳ አካሂደዋል።
በመርሃ ግብሩ የችግኝ ተከላ በቆሼ አጠቃላይ 2ተኛ ደረጃ ት/ቤት፣ የአቅመ ደካማ ቤት ግንባታ ማስጀመሪያ በኢላላ ጅረኖ ቀበሌና ለቀበሌው የሴቶች የልማት ህብረት ድጋፍ የተበረከተ ሲሆን፣ የሴቶችን የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሰሩ የሚገኙ የልማት ስራዎች የመስክ ምልከታም ተደርጓል።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሴቶችና ህፃናት ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ዘቢባ መሐመድናስር፣ በክረምት ወራት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የሴቶችና ህፃናትን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትብብር መስራት ይገባል ብለዋል።
የክልሉ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ የሰላም ተምሳሌትነትን በዘላቂነት ለማረጋገጥ በቅንጅት የተሰራው ስራ አበራታች መሆኑን የክልሉ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የህግና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አስታወቀ
የክልሉ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ የሰላም ተምሳሌትነትን በዘላቂነት ለማረጋገጥ በቅንጅት የተሰራው ስራ አበራታች መሆኑን የክልሉ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የህግና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አስታወቀ
(ሆሳዕና፦ ሀምሌ 10/2017) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ቸወካዮች ምክር ቤት የህግና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሰላምና ፀጥታ 2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምን ገምግሟል።
የክልሉ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የህግና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወ/ሮ መሰረት ወ/ሰንበት እንደገለፁት ቢሮው የሰላም ተምሳሌትነትን በዘላቂነት ለማረጋገጥ በቅንጅት የተሰራው ስራ አበራታች መሆኑን ገልፀዋል።
ቢሮው የክልሉን የሰላምና ፀጥታ ለማረጋገጥ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በተሰሩ ስራዎች ተጨባጭ ለውጦችን ለማስመዝገብ ተችሏል ነው ያሉት።
የክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ በጠንካራ የህዝብ ተሳትፎ እየተሰሩ ያሉ ፕሮጀክቶች የሚበረታታ መሆኑን የምክር ቤቱ ፕላን መሰረተ ልማትና የመንግስት ሀብት ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አስታወቀ
የክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ በጠንካራ የህዝብ ተሳትፎ እየተሰሩ ያሉ ፕሮጀክቶች የሚበረታታ መሆኑን የምክር ቤቱ ፕላን መሰረተ ልማትና የመንግስት ሀብት ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አስታወቀ
(ሆሳዕና፦ ሀምሌ 10/2017) የምክር ቤቱ ፕላን መሰረተ ልማትና የመንግስት ሀብት ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮን የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምን ገምግሟል።
ቢሮው አሰራርን በቴክኖሎጂ በማዘመን የህዝብን የመልካም አስተዳደር ቅሬታን ለመቀነስ የተሰሩ ስራዎች አበረታች ነው ብለው የቁጥጥር ስርዓቱ በማጠናከር ያስፈልጋል ብለዋል።
በጠንካራ የህዝብ ተሳትፎ እየተሰሩ ያሉ ፕሮጀክቶች ግንባታዎችን በማፋጠን የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት መስራት ያስፈልጋል።
ትርፍ መጫንና ከታሪፍ በላይ መጫንን ለማስቀረት የስምሪት መስመሮችን በኢትኬትንግ አገልግሎት እንዲሰጥ እየተደረገ ያለው ተግባር ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ነው ያሉት።
ምክር ቤቱ የፌደራል ገቢ ግብር አዋጅን አጸደቀ
ምክር ቤቱ የፌደራል ገቢ ግብር አዋጅን አጸደቀ
ሆሳዕና ፣ ሐምሌ 10፣ 2017 የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፌደራል ገቢ ግብር አዋጅን ለማሻሻል በቀረበ ረቂቅ አዋጅ ላይ ተወያይቶ አጸደቀ።
ምክር ቤቱ ዛሬ ባካሄደው ሁለተኛ አስቸኳይ ስብሰባ ነው የተሻሻውን አዋጅ ያጸደቀው።
(ኤፍ ኤም ሲ)
ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ አገልግሎቱን በማዘመን የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማሳደግ እየሰራ ያለው ተግባር አበረታች መሆኑን የምክር ቤቱ ፕላን መሰረተ ልማትና የመንግስት ሀብት ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ገለፀ
ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ አገልግሎቱን በማዘመን የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማሳደግ እየሰራ ያለው ተግባር አበረታች መሆኑን የምክር ቤቱ ፕላን መሰረተ ልማትና የመንግስት ሀብት ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ገለፀ
(ሆሳዕና፦ ሀምሌ 10/2017) የምክር ቤቱ ፕላን መሰረተ ልማትና የመንግስት ሀብት ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮን የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምን ገምግሟል።
የምክር ቤቱ ፕላን መሰረተ ልማትና የመንግስት ሀብት ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ታመነ ገብሬ ቢሮው በከተሞች ልማት እየሰራ ያለው ተግባር አበረታች ነው ብለዋል።
በከተሞች ኮርደር ልማት የተሰሩ ስራዎች አበረታች እና የህዝብን ተጠቃሚነት የሚያሳድግ በመሆኑ በተያዘለት ጊዜ ገደብ ተጠናቅቆ ለህዝቡ አገልገሎት እንዲሰጥና ቅንጅታዊ ስራዎችን ማጠናከር ይገባል ነው ያሉት።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብሄረሰቦች ምክር ቤት አባላት በሳጃ ከተማ የአረንጓዴ አሻራቸውን አኖሩ።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብሄረሰቦች ምክር ቤት አባላት በሳጃ ከተማ የአረንጓዴ አሻራቸውን አኖሩ።
(ሆሳዕና፣ሀምሌ 10/2017) ፣በምክር ቤቱ መደበኛ ጉባኤ ለመሳተፍ ሳጃ ከተማ የሚገኙት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብሄረሰቦች ምክር ቤት አባላት በከተማዋ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ ቅጥር ግቢ አረንጓዴ አሻራቸውን አሳርፈዋል።
በችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩ የክልሉ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ፣ የብሄረሰቦች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ አቡቶ አኒቶ፣ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ኤርሲኖ አቡሬ፣የየም ዞንና የሳጃ ከተማ አስተዳደር አመራሮች ተሳትፈዋል።
ምንጭ፦ የክልሉ መ/ኮ
ባሳለፍነው በጀት አመት የክልሉ ህዝቦች ህገ መንግስታዊ መብቶቻቸውን በአግባቡ እንዲጠቀሙና የጋራ እሴቶቻቸውን እንዲያጎለብቱ በልዩ ትኩረት ተሰርቷል- አቶ አቡቶ አኒቶ
ባሳለፍነው በጀት አመት የክልሉ ህዝቦች ህገ መንግስታዊ መብቶቻቸውን በአግባቡ እንዲጠቀሙና የጋራ እሴቶቻቸውን እንዲያጎለብቱ በልዩ ትኩረት ተሰርቷል- አቶ አቡቶ አኒቶ
(ሆሳዕና፣ ሀምሌ 10/2017)፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብሄረሰቦች ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤውን እያካሄደ ነው።
ባሳለፍነው በጀት አመት የክልሉ ህዝቦች ህገ መንግስታዊ መብቶቻቸውን በአግባቡ ከመጠቀም ባለፈ የጋራ እሴቶቻቸውንና ፍትሃዊ ተጠቃሚነታቸውን እያጎለበቱ እንዲሄዱ በልዩ ትኩረት መሰራቱን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብሄረሰቦች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ አቡቶ አኒቶ ተናግረዋል ።
አቶ አቡቶ የምክር ቤቱ 3ኛ ዙር 11ኛ የስራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ጉባኤ ሲካሄድ እንዳሉት ምክር ቤቱ የህዝቦችን ህገ መንግስታዊ መብቶች ከማስጠበቅ ባለፈ በጋራ እሴቶች መጎልበት፣ በሰላማዊ ግንኙነትና መስተጋብር፣ በህዝቦች አንድነት፣ የመብትና መልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን በማረጋገጥ ረገድ ግቦችን አስቀምጦ ሲሰራ ቆይቷል።