Skip to main content

የፍትህ ተቋማት ቀልጣፋና ፈጣን  የፍትህ ስርዓትን በመዘርጋት የዜጎች ህገ መንግስታዊ መብቶች እንዲከበር በቁርጠኝነት መስራት ያስፈልጋል ፦ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ

የፍትህ ተቋማት ቀልጣፋና ፈጣን  የፍትህ ስርዓትን በመዘርጋት የዜጎች ህገ መንግስታዊ መብቶች እንዲከበር በቁርጠኝነት መስራት ያስፈልጋል ፦ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ

(ነሐሴ 29/2017) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፍትህ ትራንስፎርሜሽንና የፍርድ ቤቶች ጥምረት የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸምና የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ  የምክክር መድረክ በወልቂጤ ከተማ ተካሂዷል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር  ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ  የፍትህ ተቋማት ቀልጣፋ፣ፈጣን እና ዘመናዊ የፍትህ ስርዓትን በመዘርጋት ለዜጎች ህገ መንግስታዊ መብቶች እና ነፃነት እንዲከበር በቁርጠኝነት መስራት ያስፈልጋል ብለዋል።

የስልጤ ዞን ፍትህ መምሪያ የ2017 በጀት አመት የባለሙያዎችና የአቃቤ ህጎች የማትጊያና የእውቅና መርሃ ግብር አከናወነ!

የስልጤ ዞን ፍትህ መምሪያ የ2017 በጀት አመት የባለሙያዎችና የአቃቤ ህጎች የማትጊያና የእውቅና መርሃ ግብር አከናወነ!

የስልጤ ዞን ፍትህ መምሪያ የሴክተሩን የ2017 አመታዊ አፈጻጸም መነሻ ያደረገ የባለሙያዎችና የማትጊያና የአቃቤ ህጎች የእውቅና መርሃ ግብር አከናውኗል።

በመድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት የስልጤ ዞን ፍትህ መምሪያ ሀላፊ አቶ ሬድዋን ኑሪ በ2017 መምሪያው በፈጸማቸው ተግባራትና ባስመዘገባቸው ውጤቶች ላይ የተቋሙ አጠቃላይ ሰራተኞች አሻራቸውን ማኖራቸውን አስታውቀዋል።

የተሻለ ለፈጸሙ ባለሙያዎች እውቅና መስጠትና ማበረታታት የተቋምንና የግለሰቦችን የመፈጸም አቅም እንደሚያሳደግ ያስታወሱት አቶ ሬድዋን ከዚሁ መነሻ የሴክተሩ የእውቅና አሰጣጥ መርሃ ግብር መሰናዳቱን ገልጸዋል።

በእውቅና መርሃ ግብሩ ላይ የተቋሙ አጠቃላይ ሰራተኞችና አቃቤ ህጎች በተለያዩ ዘርፎች ተከፍለው የማበረታቻ ሽልማትና የምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል።

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር )የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የተመሰረተበትን ሁለተኛ ዓመት በማስመልከት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር )የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የተመሰረተበትን ሁለተኛ ዓመት በማስመልከት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ

የመልዕክቱ ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል

ለመላዉ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሕዝቦች፣
ክልላችን ለተመሠረተበት ሁለተኛ ዓመት እንኳን አደረሳችሁ!አደረሰን !

የሉሲ(ድንቅነሽ) እና ሰላም ቅሪተ አካላት በመካከለኛው አውሮፓ በሚኖራቸው ቆይታ የኢትዮጵያን ምድረ ቀደምትነት በአዲስ መልክ ያስተዋውቃሉ - ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ

የሉሲ(ድንቅነሽ) እና ሰላም ቅሪተ አካላት በመካከለኛው አውሮፓ በሚኖራቸው ቆይታ የኢትዮጵያን ምድረ ቀደምትነት በአዲስ መልክ ያስተዋውቃሉ - ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ

ነሐሴ 9/2017)፦ የሉሲ(ድንቅነሽ) እና ሰላም ቅሪተ አካላት በመካከለኛው አውሮፓ በሚኖራቸው ቆይታ የኢትዮጵያን ምድረ ቀደምትነት በአዲስ መልክ እንደሚያስተዋውቁ የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ ገለጹ።

የቱሪዝም ሚኒስቴር ወደ ቼክ ሪፐብሊክ ለሚሄደው የሉሲ (ድንቅነሽ) እና ሰላም ቅሪተ አካላት አሸኛኘት አድርጓል።

በመርሀ ግብሩ የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ እና በኢትዮጵያ የቼክ ሪፐብሊክ አምባሳደር ሚሮስላቭ ኮሴክ ተገኝተዋል።

ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ በዚሁ ወቅት እንዳሉት ኢትዮጵያ በዓለም ከምትታወቅበት መለያ አንዱ የሰው ዘር መገኛነቷ መሆኑን ገልጸዋል።

ይህንንም ገጽታ ለመገንባት እንዲሁም ለዓለም ለማስተዋወቅ በርካታ ስራዎች መሰራታቸውን ተናግረዋል።

በመስቃንና ማረቆ በአካባቢው የተገኘው አንፃራዊ ሰላም ወደ ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እየተሰሩ ያሉ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ገለፀ።

በመስቃንና ማረቆ በአካባቢው የተገኘው አንፃራዊ ሰላም ወደ ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እየተሰሩ ያሉ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ገለፀ።

ነሀሴ 08/2017ዓ.ም ቢሮው በመስቃንና ማረቆ  አካባቢ እስካሁን ያለው የሰላምና ፀጥታ ሁኔታ አስመልክቶ የክልል ፣የዞንና ልዩ ወረዳው የፀጥታ መዋቅሮችና ኮማንድ ፖስት ጋር በቡታጅራ ከተማ ገምግሟል።

ባለፉት ጊዜያት የተሰሩ ሰላምን የማፅናት ተግባራት  ቀጣይም ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ተጠናክሮ መስራት እንደሚገባ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምናፀጥታ ቢሮና የክልሉ ፍትህ ቢሮ   ከባለድርሻ አካላት ጋር በገመገመበት ወቅት ገልጿል።

የማዕከላዊ ኢትዮያጵያ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተመስገን ካሳ እንደገለፁት  በአካባቢው የተገኘው አንፃራዊ ሰላም ወደ ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እየተሰሩ ያሉ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንደሚገባ ገልፀዋል።

የማዕከላዊ ኢትዮያጵያ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ በመስቃንና ማረቆ አካባቢ እስካሁን ያለው የሰላምና ፀጥታ ሁኔታ በቡታጅራ ከተማ እየገመገመ ነው

የማዕከላዊ ኢትዮያጵያ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ  በመስቃንና ማረቆ አካባቢ እስካሁን ያለው የሰላምና ፀጥታ ሁኔታ በቡታጅራ ከተማ እየገመገመ ነው

ነሀሴ 8/2017 የማዕከላዊ ኢትዮያጵያ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ  በመስቃንና ማረቆ  አካባቢ   እስካሁን ያለው የሰላምና ፀጥታ ሁኔታ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቡታጅራ ከተማ እየገመገመ ይገኛል።

በመድረኩ የማዕከላዊ ኢትዮያጵያ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ሀላፊና የክልሉ ኮማንድ ፖስት ሰብሳቢ አቶ ተመስገን ካሳ እና ሌሎች የሚመለከታቸው አመራሮች ተገኝተዋል።
ምንጭ :- የክልሉ መ/ኮ

የቱሪዝም ዘርፍ የገቢ ምንጭ ከመሆኑም ባለፈ ለበርካታ ወጣቶች የስራ ዕድል የሚፈጥር መሆኑን የክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ገለፀ

የቱሪዝም ዘርፍ የገቢ ምንጭ ከመሆኑም ባለፈ ለበርካታ ወጣቶች የስራ ዕድል የሚፈጥር መሆኑን የክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ገለፀ

(ነሐሴ 8/2017) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ  ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ከቱሪዝም ሚኒስቴር ጋር በመተባበር የተዘጋጀው የስልጢ_ቡታጅራ ጂኦ ፓርክ ክልላዊ ማስጀመሪያ መድረክ በወራቤ ከተማ እየተካሄደ ነው።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ሀላፊ  አቶ ሳሙኤል መንገሻ እንደተናገሩት እንደ ክልል በቱሪዝም ዘርፍ በርካታ ስራዎች እየተሰሩ ቢሆንም ከዘርፉ ማግኘት ያለበትን ጥቅም ማግኘት እንዳልተቻለ ገልፀዋል።

በክልሉ 11 የቱሪስት መስህቦችን ለማልማት ፕሮጀከት ተቀርጾ ወደ ስራ መገባቱን በመግለጽ መስህቦች ለምቶ አገልግሎት መስጠት ሲጀምር የገቢ ምንጭ ከመሆኑም ባለፈ ለበርካታ ወጣቶች የስራ ዕድል የሚፈጥር ነው ብለዋል።

ከቱሪዝም ሚኒስቴር ጋር በመተባበር የተዘጋጀው የጂኦ ፓርክ  የምክክር መድረክ ለቀጣይ ዘርፉን የበለጠ ለማሳደግ የሚረዳ እንደሆነም ተናግረዋል።

የከተማ ምግብ ዋስትናና ስራ ፕሮጀክት የ2017 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ማጠቃለያ እና የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ ማናበብ መርሃ-ግብር በዛሬው ዕለት በቡታጅራ ከተማ ተጀምሯል።

የከተማ ምግብ ዋስትናና ስራ ፕሮጀክት የ2017 በጀት ዓመት  የሥራ  አፈጻጸም ማጠቃለያ እና የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ ማናበብ መርሃ-ግብር በዛሬው ዕለት በቡታጅራ  ከተማ ተጀምሯል።

(ነሐሴ 8/2017 ) በፌዴራል መንግስትና በዓለም ባንክ ድጋፍ በተመረጡ ከተሞች ለመተግበር በተመደበው  በጀት በክልሉ ልዩ ልዩ   ፕሮጀክቶችን በማከናወንና ተጠቃሚዎችን ከተረጅነት ወደ አምራችነት ለማሸጋገር በ2017 በጀት ዓመት የተጀመረውና የተከናወኑ  የከተሞች ልማታዊ ሴፍቲኔት ስራዎች ላይ  የክልሉ ስትሪንግ ኮሚቴ አባላት እየገመገመ ነው።

በምክትል ርዕሰ መስተደድር ማዕረግ የከተማ ልማትና ኢንዱስትሪ ክላስተር አስተባባሪና የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ስንታየሁ ወልደሚካኤል የመድረኩ ዓላማ በከተማ ምግብ ዋስትናና ስራ ፕሮጀክት የተከናወኑ የ2017 በጀት ዓመት ስራዎች አፈጻጸም መገምገምና የ2018 በጀት ዓመት ዋና ዋና ዕቅዶች ላይ መናበብና የጋራ ማድረግ ነው ብለዋል።

የኢቢሲ ዲጂታል አሠራር እና የይዘት ስብጥር ለሌሎችም ሚዲያዎች አዲሱን ምዕራፍ የከፈተ ነው - ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር)

የኢቢሲ ዲጂታል አሠራር እና የይዘት ስብጥር ለሌሎችም ሚዲያዎች አዲሱን ምዕራፍ የከፈተ ነው - ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር)

(ሆሳዕና፣ ነሃሴ 7/2017)፣ የኢቢሲ ዲጂታል አሠራር እና የይዘት ስብጥር የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም የሚያስጠብቅ እና ለሌሎችም ሚዲያዎች አዲሱን ምዕራፍ የከፈተ መሆኑን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር እና የኢቢሲ ቦርድ ሰብሳቢ ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) ተናገሩ።

መረጃ የሰዎችን የዕለት ከዕለት ኑሮ በብዙ መልኩ በሚዳስስበት በዚህ ጊዜ፣ ኢቢሲ መረጃን በተለያዩ አማራጮች የሁሉንም መልክ በሚያሳይ መልኩ ተደራሽ ማድረጉ ለኢትዮጵያ ሚዲያ አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት መሆኑንም አንሥተዋል።

በማኅበራዊ ሚዲያ መረጃ በሰከንዶች ልዩነት ዓለምን በሚያካልልበት በዚህ ጊዜ የተዛቡ ትርከቶችን የሚያስተላልፉ በርካቶች እንዳሉም ሚኒስትሩ አንሥተዋል።