Skip to main content
የሥነ-ምግባር መከታተያ ክፍል ዋና ዋና ተግባርና ኃላፊነት

በደንብ ቁጥር 84/2003 ለስነምግባር መከታተያ ክፍል የተሰጠው ስልጣንና ተግባር እንደተጠበቀ ሆኖ፤

  •        በተቋሙ ውስጥ ሙስና እና ብልሹ አሰራርን መከላከል፣ 

  •        በፀረ-ሙስና፣ በሥራ ዲስፒሊን፣ በሙያ ሥነ-ምግባር፣ በሕዝብ አገልጋይነትና ኃላፊነት ስሜት ላይ የተለያዩ ትምህርትና ስልጠናዎችን በመስጠት ሙስናን መሸከም የማይችል ሠራተኛ እንዲፈጠር ጥረት ማድረግ፣

  •        የፀረ-ሙስና ፖሊሲዎችና ሕጎች መከበራቸዉን መከታተል፤ ስለ አፈጻጸማቸዉ የቢሮ ኃላፊ ማማከር፣ 

  •        የሙስና ወንጀልና ብልሹ አሰራር እንዲጋለጥ፣ እንዲመረመርና በአጥፊዎች ላይ ተገቢ እርምጃ እንዲወሰድ ጥረት ማድረግ፣

  •        የሙስና ወንጀል የሚያጋልጡ ሰራተኞች ላይ የቂም በቀል እርምጃ ለመከላከል የሚያስችል አሰራር ይዘረጋል፤ ከዚሁ ጋር በተያያዘ የበላይ አመራሩን ማማከር፣

  •        የተቋሙን የሙስና መከላከያ ስትራቴጅ ተግባራዊነት ይከታተላል፣

  •        የሥነ-ምግባር ጥሠቶችን ወይም ጥቆማዎችን ተቀብሎ በማጣራት ለበላይ አመራር የውሳኔ ሀሳብ ማቅረብ፣

  •        የተቋሙ ሠራተኞች ቅጥር፣ ዕድገት፣ ዝውውር ወይም ስልጠና እንዲሁም ማንኛዉም የግዥ አገልግሎት ከሕግና ደንብ ውጭ ተፈፅሟል ብሎ ሲያምን ማስተካከያ እንዲደረግ ከአስተያየት ጋር ለቢሮ ኃላፊ ማቅረብ፣

  •        ለሙስና እና ብልሹ አሰራር በር የሚከፍቱ አሰራሮችን በጥናት የመለየትና የመፍትሔ ሀሳብ ማቅረብ፣

  •       በስር መዋቅር የሥነ-ምግባር ኦፊሰሮች  የተሟሉ መሆኑን በማረጋገጥ መደገፍና ሥራዉን መምራት፣ 

  •        በተቋሙ በየደረጃዉ በሚሰጡ አገልግልቶች ላይ ከተገልጋዮችና ሕብረተሰቡ ጥቆማ የሚሰጥበትን ስርዓት መዘርጋት፣ ነጻ የስልክ ጥሪን እና ሌሎች አማራጮችን መፍጠር