Skip to main content

ርዕሰ መስተዳድር  እንዳሻዉ ጣሰዉ( ዶ/ር ) የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮን የሥራ ዘርፎች ሪፎርም  ለማድረግ በቀረቡ ጥናቶች ላይ ከቢሮዉ አመራሮች ጋር እየተወያዩ ነዉ፣
ሆሳዕና ፣ ሐምሌ 9፣ 2017፦ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ  ክልል መንግሥት ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻዉ ጣሰዉ( ዶ/ር ) የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮን የሥራ ዘርፎች ሪፎርም ለማድረግ በቀረቡ ጥናቶች ላይ ከቢሮዉ አመራሮች ጋር እየተወያዩ ይገኛል።

ጥናቶቹ ከተሞችንና ከተሜነትን በዘመነ መንገድ በመምራት ፣ የልማትና የመልካም አስተዳደር  እንቅስቃሴዎችን በማሳለጥ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማሻሻል የሚያስችሉ ስለመሆናቸዉ ተገልጿል ።

የጥነት ሠነዶቹ በከተምች ፈርጅ ሽግግሮችን ፣ በከተማ ተቋማዊ አደረጃጃትና አሠራሮች ማሻሻያዎችን እና  ፣በከተሞች ከመሬት ጋር የተያያዙ ህገዎጥነቶችን በመከላከል  ዙሪያ ያተኮሩ ሲሆን የጥናት ሠነዶቹ ቀርበዉ ዉይይት እየተካሄደ  ይገኛል።

ምንጭ ፦ የክልሉ መ/ኮ

Image
ርዕሰ መስተዳድር  እንዳሻዉ ጣሰዉ( ዶ/ር ) የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮን የሥራ ዘርፎች ሪፎርም  ለማድረግ በቀረቡ ጥናቶች ላይ ከቢሮዉ አመራሮች ጋር እየተወያዩ ነዉ፣