በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህግ የበላይነት እንዲረጋገጥ የተሰራው ቅንጅታዊ ስራ ትምህርት ሊወሰድበት የሚችል እንደሆነ ተገለጸ።
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህግ የበላይነት እንዲረጋገጥ የተሰራው ቅንጅታዊ ስራ ትምህርት ሊወሰድበት የሚችል እንደሆነ ተገለጸ።
ጳጉሜ 3/2017 ዓ.ም
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፍትህ ቢሮ የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም እና የ2018 ዓ/ም ዕቅድ የሚመክር ጉባኤ በቡታጅራ ከተማ እያካሄደ ይገኛል።
ጉባኤው “የህግ የበላይነትና ሰብዓዊ ክብር ያረጋገጠ የፍትህ ስርዓት እንገነባለን!” በሚል መሪ ቃል ነው ከሴክተሩ አመራር፣ ከባለድርሻ አካላት እና ከህዝብ ክንፍ አባላት እየተካሄደ የሚገኘው።
አቶ አክመል አህመዲን የክልሉ ፍትህ ቢሮ ኃላፊ ባሰሙት የመክፈቻ ንግግር የተጠናከረ ድጋፍና ክትትል በመደረጉ በሴክተሩ በተሰሩ ስራዎች ላይ ከፍ ያለ ውጤት እንዲመዘገብ ማስቻሉን ገልጸዋል።
የገዢ ትርክትን ቀጣይነት ባለው መልኩ በማስረጽና አንድነትን በማጠናከር የውስጥና የውጭ ፈተናዎችን መሻገር እንደሚገባ ተገለጸ።
የገዢ ትርክትን ቀጣይነት ባለው መልኩ በማስረጽና አንድነትን በማጠናከር የውስጥና የውጭ ፈተናዎችን መሻገር እንደሚገባ ተገለጸ።
ሀላባ: ጳጉሜ/1/2017
ጳጉሜ-1 የጽናት ቀን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሀላባ በቁሊቶ ከተማ በድምቀት ተከብሯል።
ቀኑን በክላስተሩ የሚገኙ የክልል፣ የዞን፣ የቁሊቶ ከተማ አስተዳደርና የዌራ ወረዳ የመንግስት ተቋማት ኃላፊዎች እና ሰራተኞች እንዲሁም የከተማው ማህበረሰብ በጋራ አክብረውታል።
ቀኑን አስመልክቶ ንግግር ያደረጉት የክልሉ ፍትህ ቢሮ ኃላፊ አቶ አክመል አህመዲን የጷጎሜ ቀናትን አከባበር አላማ አስረድተው፤ የዘንድሮውን የጷጎሜ ቀናት አከባበርን ልዩ የሚያደርገው ታላቁን የህዳሴ ግድብ አጠናቀን በምንመርቅበት ወቅት መሆኑ ነው ብለዋል።
በዕለቱ ልዩ ልዩ ወታደራዊ ትርኢት የቀረበ ሲሆን "ጽኑ መሠረት ብርቱ ሀገር" በሚል መሪ ቃል የፓናል ውይይት መነሻ ሰነድ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።
የፍትህ ተቋማት ቀልጣፋና ፈጣን የፍትህ ስርዓትን በመዘርጋት የዜጎች ህገ መንግስታዊ መብቶች እንዲከበር በቁርጠኝነት መስራት ያስፈልጋል ፦ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ
የፍትህ ተቋማት ቀልጣፋና ፈጣን የፍትህ ስርዓትን በመዘርጋት የዜጎች ህገ መንግስታዊ መብቶች እንዲከበር በቁርጠኝነት መስራት ያስፈልጋል ፦ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ
(ነሐሴ 29/2017) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፍትህ ትራንስፎርሜሽንና የፍርድ ቤቶች ጥምረት የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸምና የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ የምክክር መድረክ በወልቂጤ ከተማ ተካሂዷል።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ የፍትህ ተቋማት ቀልጣፋ፣ፈጣን እና ዘመናዊ የፍትህ ስርዓትን በመዘርጋት ለዜጎች ህገ መንግስታዊ መብቶች እና ነፃነት እንዲከበር በቁርጠኝነት መስራት ያስፈልጋል ብለዋል።
የስልጤ ዞን ፍትህ መምሪያ የ2017 በጀት አመት የባለሙያዎችና የአቃቤ ህጎች የማትጊያና የእውቅና መርሃ ግብር አከናወነ!
የስልጤ ዞን ፍትህ መምሪያ የ2017 በጀት አመት የባለሙያዎችና የአቃቤ ህጎች የማትጊያና የእውቅና መርሃ ግብር አከናወነ!
የስልጤ ዞን ፍትህ መምሪያ የሴክተሩን የ2017 አመታዊ አፈጻጸም መነሻ ያደረገ የባለሙያዎችና የማትጊያና የአቃቤ ህጎች የእውቅና መርሃ ግብር አከናውኗል።
በመድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት የስልጤ ዞን ፍትህ መምሪያ ሀላፊ አቶ ሬድዋን ኑሪ በ2017 መምሪያው በፈጸማቸው ተግባራትና ባስመዘገባቸው ውጤቶች ላይ የተቋሙ አጠቃላይ ሰራተኞች አሻራቸውን ማኖራቸውን አስታውቀዋል።
የተሻለ ለፈጸሙ ባለሙያዎች እውቅና መስጠትና ማበረታታት የተቋምንና የግለሰቦችን የመፈጸም አቅም እንደሚያሳደግ ያስታወሱት አቶ ሬድዋን ከዚሁ መነሻ የሴክተሩ የእውቅና አሰጣጥ መርሃ ግብር መሰናዳቱን ገልጸዋል።
በእውቅና መርሃ ግብሩ ላይ የተቋሙ አጠቃላይ ሰራተኞችና አቃቤ ህጎች በተለያዩ ዘርፎች ተከፍለው የማበረታቻ ሽልማትና የምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በመደመር ሐሳብ ላይ የጻፉት አራተኛውንና "የመደመር መንግሥት" የተሰኘውን አዲስ መጽሐፍ በተመለከተ ከፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ጋር ያደረጉት ቃለ መጠይቅ ነገ ነሐሴ 14 ቀን 2017 ዓ.ም ከምሽቱ 2:30 ይጠብቁ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በመደመር ሐሳብ ላይ የጻፉት አራተኛውንና "የመደመር መንግሥት" የተሰኘውን አዲስ መጽሐፍ በተመለከተ ከፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ጋር ያደረጉት ቃለ መጠይቅ ነገ ነሐሴ 14 ቀን 2017 ዓ.ም ከምሽቱ 2:30 ይጠብቁ።
ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር )የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የተመሰረተበትን ሁለተኛ ዓመት በማስመልከት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ
ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር )የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የተመሰረተበትን ሁለተኛ ዓመት በማስመልከት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ
የመልዕክቱ ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል
ለመላዉ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሕዝቦች፣
ክልላችን ለተመሠረተበት ሁለተኛ ዓመት እንኳን አደረሳችሁ!አደረሰን !
የሉሲ(ድንቅነሽ) እና ሰላም ቅሪተ አካላት በመካከለኛው አውሮፓ በሚኖራቸው ቆይታ የኢትዮጵያን ምድረ ቀደምትነት በአዲስ መልክ ያስተዋውቃሉ - ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ
የሉሲ(ድንቅነሽ) እና ሰላም ቅሪተ አካላት በመካከለኛው አውሮፓ በሚኖራቸው ቆይታ የኢትዮጵያን ምድረ ቀደምትነት በአዲስ መልክ ያስተዋውቃሉ - ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ
ነሐሴ 9/2017)፦ የሉሲ(ድንቅነሽ) እና ሰላም ቅሪተ አካላት በመካከለኛው አውሮፓ በሚኖራቸው ቆይታ የኢትዮጵያን ምድረ ቀደምትነት በአዲስ መልክ እንደሚያስተዋውቁ የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ ገለጹ።
የቱሪዝም ሚኒስቴር ወደ ቼክ ሪፐብሊክ ለሚሄደው የሉሲ (ድንቅነሽ) እና ሰላም ቅሪተ አካላት አሸኛኘት አድርጓል።
በመርሀ ግብሩ የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ እና በኢትዮጵያ የቼክ ሪፐብሊክ አምባሳደር ሚሮስላቭ ኮሴክ ተገኝተዋል።
ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ በዚሁ ወቅት እንዳሉት ኢትዮጵያ በዓለም ከምትታወቅበት መለያ አንዱ የሰው ዘር መገኛነቷ መሆኑን ገልጸዋል።
ይህንንም ገጽታ ለመገንባት እንዲሁም ለዓለም ለማስተዋወቅ በርካታ ስራዎች መሰራታቸውን ተናግረዋል።
በመስቃንና ማረቆ በአካባቢው የተገኘው አንፃራዊ ሰላም ወደ ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እየተሰሩ ያሉ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ገለፀ።
በመስቃንና ማረቆ በአካባቢው የተገኘው አንፃራዊ ሰላም ወደ ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እየተሰሩ ያሉ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ገለፀ።
ነሀሴ 08/2017ዓ.ም ቢሮው በመስቃንና ማረቆ አካባቢ እስካሁን ያለው የሰላምና ፀጥታ ሁኔታ አስመልክቶ የክልል ፣የዞንና ልዩ ወረዳው የፀጥታ መዋቅሮችና ኮማንድ ፖስት ጋር በቡታጅራ ከተማ ገምግሟል።
ባለፉት ጊዜያት የተሰሩ ሰላምን የማፅናት ተግባራት ቀጣይም ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ተጠናክሮ መስራት እንደሚገባ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምናፀጥታ ቢሮና የክልሉ ፍትህ ቢሮ ከባለድርሻ አካላት ጋር በገመገመበት ወቅት ገልጿል።
የማዕከላዊ ኢትዮያጵያ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተመስገን ካሳ እንደገለፁት በአካባቢው የተገኘው አንፃራዊ ሰላም ወደ ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እየተሰሩ ያሉ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንደሚገባ ገልፀዋል።
የማዕከላዊ ኢትዮያጵያ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ በመስቃንና ማረቆ አካባቢ እስካሁን ያለው የሰላምና ፀጥታ ሁኔታ በቡታጅራ ከተማ እየገመገመ ነው
የማዕከላዊ ኢትዮያጵያ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ በመስቃንና ማረቆ አካባቢ እስካሁን ያለው የሰላምና ፀጥታ ሁኔታ በቡታጅራ ከተማ እየገመገመ ነው
ነሀሴ 8/2017 የማዕከላዊ ኢትዮያጵያ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ በመስቃንና ማረቆ አካባቢ እስካሁን ያለው የሰላምና ፀጥታ ሁኔታ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቡታጅራ ከተማ እየገመገመ ይገኛል።
በመድረኩ የማዕከላዊ ኢትዮያጵያ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ሀላፊና የክልሉ ኮማንድ ፖስት ሰብሳቢ አቶ ተመስገን ካሳ እና ሌሎች የሚመለከታቸው አመራሮች ተገኝተዋል።
ምንጭ :- የክልሉ መ/ኮ
የቱሪዝም ዘርፍ የገቢ ምንጭ ከመሆኑም ባለፈ ለበርካታ ወጣቶች የስራ ዕድል የሚፈጥር መሆኑን የክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ገለፀ
የቱሪዝም ዘርፍ የገቢ ምንጭ ከመሆኑም ባለፈ ለበርካታ ወጣቶች የስራ ዕድል የሚፈጥር መሆኑን የክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ገለፀ
(ነሐሴ 8/2017) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ከቱሪዝም ሚኒስቴር ጋር በመተባበር የተዘጋጀው የስልጢ_ቡታጅራ ጂኦ ፓርክ ክልላዊ ማስጀመሪያ መድረክ በወራቤ ከተማ እየተካሄደ ነው።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ሀላፊ አቶ ሳሙኤል መንገሻ እንደተናገሩት እንደ ክልል በቱሪዝም ዘርፍ በርካታ ስራዎች እየተሰሩ ቢሆንም ከዘርፉ ማግኘት ያለበትን ጥቅም ማግኘት እንዳልተቻለ ገልፀዋል።
በክልሉ 11 የቱሪስት መስህቦችን ለማልማት ፕሮጀከት ተቀርጾ ወደ ስራ መገባቱን በመግለጽ መስህቦች ለምቶ አገልግሎት መስጠት ሲጀምር የገቢ ምንጭ ከመሆኑም ባለፈ ለበርካታ ወጣቶች የስራ ዕድል የሚፈጥር ነው ብለዋል።
ከቱሪዝም ሚኒስቴር ጋር በመተባበር የተዘጋጀው የጂኦ ፓርክ የምክክር መድረክ ለቀጣይ ዘርፉን የበለጠ ለማሳደግ የሚረዳ እንደሆነም ተናግረዋል።