Seble
Thu, 07/17/2025 - 10:30
ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በሆሳዕና ከተማ የኮሪደር ልማት እና አስፋልት መንገድ ስራ አስመልክቶ በጽ/ቤታቸው ውይይት እያካሔዱ ነው
(ሆሳዕና ፣ሐምሌ 10/2017)የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)ከሀዲያ ዞን እና ከሆሳዕና ከተማ አመራሮች ጋር በሆሳዕና ከተማ የኮሪደር ልማት እና የአስፋልት መንገድ ስራ አስመልክቶ በጽ/ቤታቸው ውይይት እያካሔዱ ነው።
በመድረኩ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የከተማ ልማትና ኢንዱስትሪ ክላስተር አስተባባሪና የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ስንታየሁ ወ/ሚካኤል ተገኝተዋል።
በሆሳዕና ከተማ ግንባታው እየተካሔደ የሚገኘው የኮሪደር ልማት ስራ ከፍሳሽ ማስወገጃ ቦይ ጋር ተቀናጅቶ ተፈጻሚ መሆን በሚችልበት ጉዳይ ላይ ርዕሰ መስተዳድሩ እየገመገሙ ነው።
በክልሉ 165 ኪ/ሜ የኮሪደር ልማት ግንባታ ለማካሔድ እየተሰራ መሆኑ ይታወሳል።
ምንጭ :-. የክልሉ መ/ኮ
Image
