Thu, 06/27/2024 - 12:17
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ ፍትህ ቢሮ የታችኛው መዋቅሮች የበጀት ዓመት ማጠቃለያ ድጋፍ እና ክትትል ሪፖርት ግምገማ በዛሬዉ ዕለት አካሄዶል።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፍትህ ቢሮ ለታችኛው መዋቅር የ2016 በጀት አመት ማጠቃለያ ድጋፍና ክትትል ማድረጉ ይታወቃል። ከድጋፍ ክትትሉ መልስ በዛሬው ዕለት ከቢሮ ኃላፊዎችና ከማንጅመንት አባላት ጋር ሪፖርቱን በመገምገም በጥንካሬና በድክመት በታዩ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ሃሳቦች ከተነሱ በኃላ ለመዋቅሮችም ግብረ መልስ እንዲሰጥባቸው በመወሰን ; ይህም የፍትህ ስርዓቱን እና አጠቃላይ አሰራርን ለማሻሻል ከሚያደርጉ ጥረቶች አንዱ አካል እንደሆነም ተገልጾል።
የፍትህ ቢሮ የመንግስት ኮሙኔኮሽን!
Image
