የዓቃቢያነ ህግ አስተዳደር ዋና ጉባኤ ጽ/ቤት ዋና ዋና ተግባርና ኃላፊነትከዓቃቤ ሕግ አስተዳደር ዋና ጉባኤ ጋር በመሆን የዓቃብያነ ሕግ ሹመት፣ ዝውውር፣ የዕረፍትጊዜ፣ የአገልግልት ዘመን፣ ደረጃ፣ ሥነምግባር፣ አደረጃጀት፣ መዋቅር፣ ደመወዝ፣ ጥቅማ ጥቅም እና የመሳሰለ ጉዳዩችን ያካተተ ረቂቅ ደንብ አዘጋጅቶ ለዋና ጠቅላይ ዓቃቤ ሕጉ በማቅረብ በዋና ጉባኤ ተተችቶ ለመስተዳድር ም/ቤት እንዲቀርብ ያደርጋል፡፡
በዋናው ጉበኤ የሚሰጡትን የተለያዩ ስራዎች ጨምሮ የዓቃብያነ ህጉን መረጃ በአግባቡ የመያዝ እና አስተዳደራዊ አገልግልቶችን ይሰጣል፡፡
ዐቃበያነ ህግ አስተዳደር ጉባኤ የሚወስናቸውን እና የሚሰጣቸውን ውሳኔዎች እና ትዕዛዞች አፈጻፀም መከታተልና ሲፈለግ ለጉባኤው ያቃርባል፡፡
በዐቃብያነ ህግ የሚቀርቡ የዲስፕሊን ጉዳዮችን በማደራጀት ለቢሮ ኃላፊ በማቅረብ የሚፈቱበትን ሁኔታዎች ማማከር፣ የዐቃቢያነ ህግመብት ጥያቄዎችን በመቀበል ለቢሮኃላፊ በማቅረብ በዋናዉ ጉባኤየሚወስንበትን ሁኔታ ማመቻቸት፣ የክልሉን ዐቃብያነ ህግማስተዳደር ጋር ተያይዞ በዋና ጠቅላይ ዓቃቤ ህጉ የሚሰጡ ማንኛዉንም ህጋዊ ትዕዛዝ መፈጸምና ማማከር፡፡