የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የአስፈጻሚ አካላት የበጀት ዓመቱን ዕቅድ አፈጻጸም እየገመገመ ነው።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የአስፈጻሚ አካላት የበጀት ዓመቱን ዕቅድ አፈጻጸም እየገመገመ ነው።
(ሆሳዕና፦ሀምሌ 7/2017) በምክር ቤቱ ፕላን መሰረተ ልማትና የመንግስት ሀብት ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የክልሉን ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ የበጀት ዓመቱን ዕቅድ አፈጻጸምን በወልቂጤ ከተማ ገምግሟል።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ፕላን መሰረተ ልማትና የመንግስት ሀብት ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ታመነ ገብሬ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ህብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ በርካታ ስራዎች ተሰርቷል ብለዋል።
ቢሮው በበጀት ዓመቱ ያከናወናቸው ሰው ተኮር ተግባራት የሚያበረታታ እንደሆነም ገልፀዋል።
የህብረተሰቡን ኑሮ ውድነትን ለመቀነስ የተጀመረው የሰንበት ገበያ ስራን በማጠናከር አቅራቢውን እና ሸማቹን ማህበረሰብ ተጠቃሚ እያደረገ በመሆኑ ለጥራቱ በልዩ ትኩረት ተሰጥቶ ሊሰራ ይገባል ነው ያሉት።
በክልሉ የህዝብ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ በሚያስችሉ ተግባራት ላይ በትኩረት መስራት ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻዉ ጣሰዉ (ዶ/ር)
በክልሉ የህዝብ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ በሚያስችሉ ተግባራት ላይ በትኩረት መስራት ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻዉ ጣሰዉ (ዶ/ር)
(ሆሳዕና፣ሐምሌ 7/2017)የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻዉ ጣሰዉ (ዶ/ር )ከዞኖችና ከልዩ ወረዳ አመራሮች ጋር በጽ/ቤታቸው እየመከሩ ነው
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻዉ ጣሰዉ (ዶ/ር በምክክር መድረኩ እንደገለጹት የክልሉን መንግስት የ2017 በጀት አመት አፈጻጸም አስመልክቶ በቀረበው ሪፖርት ላይ ውይይት ይካሔዳል ብለዋል።
በክልሉ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገር የተከናወኑ ስራዎች ሪፖርት፣የፋይዳ ብሔራዊ መታወቂያ፣የ5 ሚሊየን ኮደርስ፣የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች ቀን በአል አከባበር የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እና በሌሎችም አጀንዳዎች ላይ የጋራ መግባባት መፍጠር የሚያስችል መድረክ ስለመሆኑም ርዕሰ መስተዳድሩ አብራርተዋል።
የሴቶችና ህፃናትን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በቅንጅት መስራት ያስፋልጋል - ወ/ሮ ሂክማ ከይረዲን
የሴቶችና ህፃናትን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በቅንጅት መስራት ያስፋልጋል - ወ/ሮ ሂክማ ከይረዲን
የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር አመራሮች እና ባለሙያዎች በክልሉ በሴቶችና ህጻናት ዘርፍ የተከናወኑ ተግባራትን ምልከታ አድርገዋል።
(ሆሳዕና፦ ሀምሌ 6/2017) ፣ የኢፌዴሪ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር አመራሮችና ባለሙያዎች ቡድን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጉራጌ ዞን በሴቶችና ህፃናት ዘርፍ የተሰሩ ተግባራትን ነው ምልከታ ያደረገው።
የኢፌዴሪ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ሴቶችና ህፃናት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሂክማ ከይረዲን እንደተናገሩት ከድህነት ለመላቀቅ በሴቶች ህብረት መደራጀት የሴቶችን ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ተጠቃሚነት እያሳደገ ነው ብለዋል።
ሴቶች የኢትዮጵያን ብልጽግና የሚያረጋግጡ ናቸው ያሉት ወ/ሮ ሂክማ የሴቶችንና ህፃናትን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ በቅንጅት መስራት ያስፈልጋል ሲሉም ተናግረዋል።
በመኸር እርሻ እስካሁን 7 ሚሊየን ሄክታር በዘር ተሸፍኗል::
በመኸር እርሻ እስካሁን 7 ሚሊየን ሄክታር በዘር ተሸፍኗል
ሆሳዕና ፣ ሐምሌ 6፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ2017/18 የመኸር ወቅት እርሻ እስካሁን 7 ሚሊየን ሄክታር መሬት በዘር ተሸፍኗል አሉ የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር)።
ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) እንዳሉት ÷ በግብርናው ዘርፍ በመኸር፣ በበልግ እንዲሁም በመስኖ ልማት ሥራዎች ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ ሥራዎች አመርቂ ውጤት ተመዝግቧል፡፡
በዚህ ዓመት በመላ ሀገሪቱ 21 ሚሊየን ሄክታር መሬት በመኸር እርሻ በተለያዩ ሰብሎች በዘር እንደሚሸፈን ነው የተናገሩት፡፡
አሁን ላይ በከፍተኛ ሁኔታ የዘር ሥራ የሚከናወንበት በመሆኑ እንደ በቆሎ ያሉ የአገዳ ሰብሎች ቀድሞ መዘራታችን ጠቁመው÷ ጤፍ፣ ስንዴ፣ ገብስና ሌሎች እንደየ አካባቢው ሥነ ምህዳር እየተዘሩ ነው ብለዋል፡፡
ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም እና ለአርሶ አደሩ ግንዛቤ በመፍጠር ጭምር በመሰራቱ በዚህ ዓመት የተሻለ ምርት ይጠበቃል ነው ያሉት፡፡
የምስራቅ ጉራጌ ዞን የ2017 ዞናዊ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በሶዶ ወረዳ ጢያ ከተማ "በመትከል ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል የችግኝ ተከላ እየተካሄደ ነው::
የምስራቅ ጉራጌ ዞን የ2017 ዞናዊ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በሶዶ ወረዳ ጢያ ከተማ "በመትከል ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል የችግኝ ተከላ እየተካሄደ ነው።
(ሆሳዕና፣ሐምሌ 06/2017)፣ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የገጠር ልማት ክላስተር አስተባባሪ እና የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኡስማን ሱሩርና የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙስጠፋ ሀሰን ዞናዊ የአረንጓዴ አሻራ ፕሮግራም በሶዶ ወረዳ ጢያ ከተማ አስጀምረዋል።በዕለቱ ለምግብነት የሚውሉ አትክልትና ፍራፍሬዎች በመትከል አሻራቸውን አኑረዋል።በዘንድሮው ዓመት በዞኑ ከሀያ አምስት ሚሊየን ችግኝ ሁሉም የማህበረሰብ ክፍሎች በማሳተፍ የተለያዩ ጠቀሜታ ያላቸው ፍራፍሬና አትክልቶች እንደሚተከሉ ተጠቅሷል።በመረሃ ግብሩ የዞኑ፣የወረዳውና የከተማ አስተዳደር አመራሮችና ነዋሪዎች አሻራቸውን ማኖራቸውን ከዞኑ የመንግስት ኮሙኒኬሽን መምሪያ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።
ምንጭ :- የክልሉ መ/ኮ
#የሳምንቱ #አበይት #ዜናዎቻችን....
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) የ12ኛ ክፍል የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎችን ብሄራዊ ፈተና በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የፈተና ማዕከል አስጀመሩ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ከዛሬ ጀምሮ ባሉት ሶስት ተከታታይ ቀናት የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ብሄራዊ ፈተናን በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የፈተና ማዕከል አስጀምረዋል።
ርዕሰ መስተዳድሩ በዚሁ ወቅት ለተማሪዎቹ መልካም ውጤት ተመኝተዋል።
.......................................//.........................................
የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም እና በምግብ እራስን ለመቻል የተጀመረው ዘመቻ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት - ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻዉ ጣሰዉ (ዶ/ር)
#የሳምንቱ #አበይት #ዜናዎቻችን....
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) የ12ኛ ክፍል የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎችን ብሄራዊ ፈተና በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የፈተና ማዕከል አስጀመሩ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ከዛሬ ጀምሮ ባሉት ሶስት ተከታታይ ቀናት የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ብሄራዊ ፈተናን በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የፈተና ማዕከል አስጀምረዋል።
ርዕሰ መስተዳድሩ በዚሁ ወቅት ለተማሪዎቹ መልካም ውጤት ተመኝተዋል።
.......................................//.........................................
የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም እና በምግብ እራስን ለመቻል የተጀመረው ዘመቻ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት - ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻዉ ጣሰዉ (ዶ/ር)
የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት አስጀመረ
የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት አስጀመረ
ሆሳዕና ፣ ሐምሌ 5፣ 2017 የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ከተጠሪ ተቋማት ጋር በመሆን የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎትን በጉራጌ ዞን አበሽጌ ወረዳ አስጀምሯል፡፡
በመርሐ ግብሩ ላይ የጽ/ቤት ኃላፊ እና የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር አለምጸሀይ ጳውሎስን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ሀላፊዎች ተገኝተዋል።
በማስጀመሪያው የአቅመ ደካሞችን ቤት የማደስ እና የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ችግኝ ተከላ ተካሂዷል።
በተጨማሪም በአበሽጌ ወረዳ የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤት ግንባታ፣ የአቅመ ደካሞች የመኖሪያ ቤት ግንባታ እና የጽዱ ኢትዮጵያ ኢኒሼቲቭ አካል የሆነው የመጸዳጃ ቤት ግንባታ ተጀምሯል፡፡
የሥራ ኃላፊዎቹ በዞኑ እየተሰሩ ያሉ የልማት ስራዎችን ጎብኝተዋል ሲል ኤፍ ኤም ሲ ዘግቧል።
በተጠናቀቀዉ በጀት ዓመት በክልሉ ተግባራትን በቅንጅት፣ በእዉቀትና በክህሎት የመፈጸምና የማስፈፀም ልምምድ እየተሻሻለ መጥቷል፤ የተናጠልና የቡድን ሀላፊነትን የመወጣት ዝግጁነትና ጥረትም እየጎለበተ ይገኛል።
በተጠናቀቀዉ በጀት ዓመት በክልሉ ተግባራትን በቅንጅት፣ በእዉቀትና በክህሎት የመፈጸምና የማስፈፀም ልምምድ እየተሻሻለ መጥቷል፤ የተናጠልና የቡድን ሀላፊነትን የመወጣት ዝግጁነትና ጥረትም እየጎለበተ ይገኛል።
እንዳሻዉ ጣሰዉ (ዶ/ር)የማዕከላዊ ኢትዮጵያዊ ክልል መንግስት ርዕሰ መስተዳድር ፣
ምንጭ፦ የክልሉ መ/ኮ
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የወጣቶች የክረምት ወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በይፋ ተጀመረ
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የወጣቶች የክረምት ወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በይፋ ተጀመረ
(ሆሳዕና፣ ሀምሌ 4/2017)፣ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከመላው ኢትዮጵያ ለተወጣጡ የክረምት ወሰን ተሻጋሪ በጎ ፈቃድ አገልግሎት ተሳታፊ ወጣቶች በሆሳዕና ከተማ አቀባበል ተደርጓል።
"በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ ቃል ለ4ኛ ጊዜ የሚካሄደው ሀገር አቀፍ የወሰን ተሻጋሪ የክረምት ወራት በጎ ፈቃደኛ ወጣቶች አገልግሎት በክልሉ መካሄድ ጀምሯል።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጌታቸው ሌሊሾ ወጣቶቹን የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ባስተላለፉት ወቅት፣ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ዓለማ፤ ወጣቶችንና ሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎችን በስፋት እንዲሳተፉ በማድረግ የማህበረሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን በመፍታትና የበጎ ፈቃደኝነት አገልግሎት ባህል ሆኖ እንዲጎለብት የማድረግ ሚናን መጨወት መሆኑን ተናግረዋል።