የ 2018 ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ በሠላም እንዲጠናቀቅ ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ የማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል ፍትህ ቢሮ አስታወቀ።
የ 2018 ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ በሠላም እንዲጠናቀቅ
ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ የማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል ፍትህ ቢሮ አስታወቀ።
መጋቢት:-15 /2018 ዓ.ም
የክልሉ ፍትህ ቢሮ በምርጫ ህግ ፤ በጥላቻ ንግግር እና ሀሰተኛ መረጃ ስርጭትን በመከላከል ዙሪያ ያተኮረ የምክክር መድረክ በቡታጀራ ከተማ አካሂዷል።
በመርሀ ግብሩም ከዞንና ከልዩ ወረዳ ፍርድ ቤቶች የተውጣጡ ዳኞች፣ ከፍትሕ መምሪያዎች የተወከሉ ዓቃቢያነ ሕግ፣ ከፖሊስ መምሪያዎች የተገኙ መርማሪ ፖሊሶች እና የሲቪክ ማኅበራት ተወካዮች ተሳትፈዋል።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፍትህ ቢሮ የዐቃቢያነ -ህግ የሙያ ሥነ-ምግባር ረቂቅ መመሪያ ለማሻሻል ከቢሮው ዐቃቢያነ ህጎች ጋር ውይይት አደረገ።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፍትህ ቢሮ የዐቃቢያነ -ህግ የሙያ ሥነ-ምግባር ረቂቅ መመሪያ ለማሻሻል ከቢሮው ዐቃቢያነ ህጎች ጋር ውይይት አደረገ።
ሀላባ መጋቢት 1/2018 ዓ.ም
ቢሮው የ0ቃ ቢያነ - ህግ የሙያ ሥነ - ምግባር ረቂቅ መመሪያን በማዘጋጀት ከቢሮው ዐቃቤ ህጎች ጋር በመወያየት ረቂቁን በተሻለ ለማጎልበት አጋዥ የሚሆኑ ግብዓቶችን ለማግኘት በተደረገው የውይይት መድረክ ላይ ከተወያይዎች ጠቃሚና ገንቢ ሀሳቦች ተሰንዝረዋል። ረቂቁን ባዘጋጁት ቡድኖችም ከቤቱ ለተነሱ ጥያቄዎች እና አስተያየቶች ተገቢውን ምላሽ በመስጠት ረቂቁን በቀጣይ ለማሻሻል ወሳኝ ግብዓቶች ማግኘታቸውን ገልፀዋል።
ለዘገባው የቢሮው መ/ኮ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፍትህ ቢሮ ''ከአኩሪ ታሪከ ፣ ወደ ብሩ አድማስ'' በሚል መሪ ቃል 130ኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት አከበረ።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፍትህ ቢሮ '' ከአኩሪ ታሪከ ፣ ወደ ብሩ አድማስ'' በሚል መሪቃል 130ኛ ውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት አከበረ።
ጥቃትን የማይታገስ ማህበረሰብ ለሀገር ግንባታ" በሚል መሪ ቃል የጸረ ፆታዊ ጥቃት የነጭ ሪቫን ቀን ተከበረ
"ጥቃትን የማይታገስ ማህበረሰብ ለሀገር ግንባታ" በሚል መሪ ቃል የጸረ ፆታዊ ጥቃት የነጭ ሪቫን ቀን ተከበረ
***
ታህሳስ 8/2018
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፍትህ ቢሮ ''
''ጥቃትን የማይታገስ ማህበረሰብ ለሀገር ግንባታ'' በሚል መርህ ቃል በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ34ኛ ግዜ በሀገራችንና በክልላችን ለ20ኛ ጊዜ የሚከበረው የነጭ ሪቫን ቀን በሀላባ ቁሊቶ ከተማ ተከበረ።
በመክፈቻ ንግግር መድረኩን ያስጀመሩት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፍትህ ቢሮ ምክትል ሃላፊ አቶ ኢያሱ ሻንቆ በበኩላቸው የሴቶች ጥቃት በአለም አቀፍ በተለያዩ መልኩ የሚፈጸምና በሰዎች አካል ፣ህይወት እና ንብረት ላይ ጉዳት የሚደርስ ድርጊት መሆኑን ገልፀዋል።
ምክትል ሃላፊ አቶ ኢያሱ ሻንቆ አያይዘውም አካላዊ ፣ስሜታዊ ፣ ሥነልቦናዊ ኢኮኖሚያዊ ማህበራዊ ጉዳት የመብት ጥሰት በማድረስ የሚፈጸም እኩይ ድርጊት መሆኑን ጠቁመ፣
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፍትህ ቢሮ የ 2018 በጀት አመት 1ኛ ሩብ አመት ዕቅድ አፈፃፀም ገመገመ።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፍትህ ቢሮ የ 2018 በጀት አመት 1ኛ ሩብ አመት ዕቅድ አፈፃፀም ገመገመ።
(ሀላባ፣ ጥቅምት 8/ 2018 )
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፍትህ ቢሮ ከተጠሪ ተቋማት ፣ ከዞን ፍትህ መምሪያ እና ከልዩ ወረዳ ፍትህ ጽ/ቤት ጋር የበጀት አመቱን 1ኛ ሩብ አመት ዕቅድ አፈፃፀም በሀላባ ቁሊቶ ከተማ ገምግሟል።
በመድረኩ የቢሮው ኃላፊ አቶ አክመል አህመዲን፣ የዜጎች ሰብዓዊ መብት እንዲከበር፣ ወንጀልን በመከላከል፣ የህግ የበላይነት እንዲረጋገጥ እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል።
በማከልም በፍትህ ተቋማት አሰራርን ከማዘመን አንፃር የሚስተዋሉ ጉድለቶችን ለመቅረፍ እየተሰራ መሆኑን የጠቆሙት የቢሮ ኃላፊው የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመቅረፍ የህዝብ እርካታን ከፍ ለማድረግ መሥራት እንደሚገባ ጠቅሰዋል።
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህግ የበላይነት እንዲረጋገጥ የተሰራው ቅንጅታዊ ስራ ትምህርት ሊወሰድበት የሚችል እንደሆነ ተገለጸ።
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህግ የበላይነት እንዲረጋገጥ የተሰራው ቅንጅታዊ ስራ ትምህርት ሊወሰድበት የሚችል እንደሆነ ተገለጸ።
ጳጉሜ 3/2017 ዓ.ም
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፍትህ ቢሮ የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም እና የ2018 ዓ/ም ዕቅድ የሚመክር ጉባኤ በቡታጅራ ከተማ እያካሄደ ይገኛል።
ጉባኤው “የህግ የበላይነትና ሰብዓዊ ክብር ያረጋገጠ የፍትህ ስርዓት እንገነባለን!” በሚል መሪ ቃል ነው ከሴክተሩ አመራር፣ ከባለድርሻ አካላት እና ከህዝብ ክንፍ አባላት እየተካሄደ የሚገኘው።
አቶ አክመል አህመዲን የክልሉ ፍትህ ቢሮ ኃላፊ ባሰሙት የመክፈቻ ንግግር የተጠናከረ ድጋፍና ክትትል በመደረጉ በሴክተሩ በተሰሩ ስራዎች ላይ ከፍ ያለ ውጤት እንዲመዘገብ ማስቻሉን ገልጸዋል።
የገዢ ትርክትን ቀጣይነት ባለው መልኩ በማስረጽና አንድነትን በማጠናከር የውስጥና የውጭ ፈተናዎችን መሻገር እንደሚገባ ተገለጸ።
የገዢ ትርክትን ቀጣይነት ባለው መልኩ በማስረጽና አንድነትን በማጠናከር የውስጥና የውጭ ፈተናዎችን መሻገር እንደሚገባ ተገለጸ።
ሀላባ: ጳጉሜ/1/2017
ጳጉሜ-1 የጽናት ቀን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሀላባ በቁሊቶ ከተማ በድምቀት ተከብሯል።
ቀኑን በክላስተሩ የሚገኙ የክልል፣ የዞን፣ የቁሊቶ ከተማ አስተዳደርና የዌራ ወረዳ የመንግስት ተቋማት ኃላፊዎች እና ሰራተኞች እንዲሁም የከተማው ማህበረሰብ በጋራ አክብረውታል።
ቀኑን አስመልክቶ ንግግር ያደረጉት የክልሉ ፍትህ ቢሮ ኃላፊ አቶ አክመል አህመዲን የጷጎሜ ቀናትን አከባበር አላማ አስረድተው፤ የዘንድሮውን የጷጎሜ ቀናት አከባበርን ልዩ የሚያደርገው ታላቁን የህዳሴ ግድብ አጠናቀን በምንመርቅበት ወቅት መሆኑ ነው ብለዋል።
በዕለቱ ልዩ ልዩ ወታደራዊ ትርኢት የቀረበ ሲሆን "ጽኑ መሠረት ብርቱ ሀገር" በሚል መሪ ቃል የፓናል ውይይት መነሻ ሰነድ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።
የፍትህ ተቋማት ቀልጣፋና ፈጣን የፍትህ ስርዓትን በመዘርጋት የዜጎች ህገ መንግስታዊ መብቶች እንዲከበር በቁርጠኝነት መስራት ያስፈልጋል ፦ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ
የፍትህ ተቋማት ቀልጣፋና ፈጣን የፍትህ ስርዓትን በመዘርጋት የዜጎች ህገ መንግስታዊ መብቶች እንዲከበር በቁርጠኝነት መስራት ያስፈልጋል ፦ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ
(ነሐሴ 29/2017) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፍትህ ትራንስፎርሜሽንና የፍርድ ቤቶች ጥምረት የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸምና የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ የምክክር መድረክ በወልቂጤ ከተማ ተካሂዷል።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ የፍትህ ተቋማት ቀልጣፋ፣ፈጣን እና ዘመናዊ የፍትህ ስርዓትን በመዘርጋት ለዜጎች ህገ መንግስታዊ መብቶች እና ነፃነት እንዲከበር በቁርጠኝነት መስራት ያስፈልጋል ብለዋል።
የስልጤ ዞን ፍትህ መምሪያ የ2017 በጀት አመት የባለሙያዎችና የአቃቤ ህጎች የማትጊያና የእውቅና መርሃ ግብር አከናወነ!
የስልጤ ዞን ፍትህ መምሪያ የ2017 በጀት አመት የባለሙያዎችና የአቃቤ ህጎች የማትጊያና የእውቅና መርሃ ግብር አከናወነ!
የስልጤ ዞን ፍትህ መምሪያ የሴክተሩን የ2017 አመታዊ አፈጻጸም መነሻ ያደረገ የባለሙያዎችና የማትጊያና የአቃቤ ህጎች የእውቅና መርሃ ግብር አከናውኗል።
በመድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት የስልጤ ዞን ፍትህ መምሪያ ሀላፊ አቶ ሬድዋን ኑሪ በ2017 መምሪያው በፈጸማቸው ተግባራትና ባስመዘገባቸው ውጤቶች ላይ የተቋሙ አጠቃላይ ሰራተኞች አሻራቸውን ማኖራቸውን አስታውቀዋል።
የተሻለ ለፈጸሙ ባለሙያዎች እውቅና መስጠትና ማበረታታት የተቋምንና የግለሰቦችን የመፈጸም አቅም እንደሚያሳደግ ያስታወሱት አቶ ሬድዋን ከዚሁ መነሻ የሴክተሩ የእውቅና አሰጣጥ መርሃ ግብር መሰናዳቱን ገልጸዋል።
በእውቅና መርሃ ግብሩ ላይ የተቋሙ አጠቃላይ ሰራተኞችና አቃቤ ህጎች በተለያዩ ዘርፎች ተከፍለው የማበረታቻ ሽልማትና የምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በመደመር ሐሳብ ላይ የጻፉት አራተኛውንና "የመደመር መንግሥት" የተሰኘውን አዲስ መጽሐፍ በተመለከተ ከፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ጋር ያደረጉት ቃለ መጠይቅ ነገ ነሐሴ 14 ቀን 2017 ዓ.ም ከምሽቱ 2:30 ይጠብቁ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በመደመር ሐሳብ ላይ የጻፉት አራተኛውንና "የመደመር መንግሥት" የተሰኘውን አዲስ መጽሐፍ በተመለከተ ከፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ጋር ያደረጉት ቃለ መጠይቅ ነገ ነሐሴ 14 ቀን 2017 ዓ.ም ከምሽቱ 2:30 ይጠብቁ።