ከፍተኛ ጉዳት እያደረሰ የሚገኘውን ኢ-መደበኛ ፍልሰትና በሰው መነገድ ወንጀል ለመከላከል የህግ ማዕቀፍ ማጠናከርን ያማከለ የምክክር መድረክ ተካሄደ
ከፍተኛ ጉዳት እያደረሰ የሚገኘውን ኢ-መደበኛ ፍልሰትና በሰው መነገድ ወንጀል ለመከላከል የህግ ማዕቀፍ ማጠናከርን ያማከለ የምክክር መድረክ ተካሄደ
ሀላባ ግንቦት 4/2018 ዓ.ም
የማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል መንግስት ፍትህ ቢሮ ኢ-መደበኛ ፍልሰትን፣ በሰው መነገድን እና ህገ-ወጥ የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የወጣውን አዋጅ ቁጥር 1178/2012 እና ደንብ ቁጥር 32/2017 አስመልክቶ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር የምክክርና የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ በዱራሜ ከተማ ተካሂዷል።
በሴቶችና ህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ወንጀሎችን መከላከል እና ምላሽ አሰጣጥ ዙርያ የአቅም ግንባታ ሥልጠና ተሰጠ።
በሴቶችና ህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ወንጀሎችን መከላከል እና ምላሽ አሰጣጥ ዙርያ የአቅም ግንባታ ሥልጠና ተሰጠ።
*****
ሚያዝያ 20 / 2018 ዓ.ም ሀላባ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፍትህ ቢሮ በሴቶችና ህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ወንጀሎችን ለመከላከል እና ድርጊቱ ሲፈፀም ፈጣንና ፍትሃዊ ምላሽ ለመስጠት ያለመ የአቅም ግንባታ ሥልጠና በወራቤ ከተማ ተሰጠ።
በሥልጠናው በሴቶችና ህጻናት ላይ የሚፈፀሙ ወንጀሎች በተለይ የሴት ልጅ ግርዛትና ያለ-እድሜ ጋብቻን ለመከላከል እና ተፈጽሞ ሲገኝ ተገቢውን ምላሽ በመስጠት የሚሰሩ ዐቃቤያነ-ህጎች፣ መርማሪ ፖሊሶች እና የማህበራዊ ሳይንስ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ፍትህ ቢሮ የ9 ወር ዕቅድ አፈፃፀም በጥልቀት ገመገመ።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ፍትህ ቢሮ የ9 ወር ዕቅድ አፈፃፀም በጥልቀት ገመገመ።
ሀላባ፣ ሚያዚያ 8/2018 ዓ.ም
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፍትህ ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት የ9 ወራት ዕቅድ አፈፃፀሙን ከአመራሮችና ከማናጅመንት አካላት ጋር በመሆን በጥልቀት ገምግሟል።
በዚሁ የግምገማ መድረክ የቢሮው ኃላፊ አቶ አክመል አህመዲን የተገኙ ሲሆን፣ የ9 ወራት አፈፃፀም ሪፖርቱ በልማት ዕቅድ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር በአቶ ጌታሁን ፍቅሩ በተደራጀ ሁኔታ ቀርቧል።
በቀረበው ሪፖርት ላይ አመራሮችና ማናጅመንት አባላት ጥልቅ ውይይት በማካሄድ ጠንካራ አፈፃፀሞችን እና የሚሻሻሉ ዘርፎችን ለይተው ገንቢ አስተያየት አቀርበዋል።
በመጨረሻም የቢሮው ኃላፊ አቶ አክመል አህመዲን ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎችን በግልፅ በማብራራት፣ በተለይም የተገኙ ውጤቶችን ማጠናከር እና የታዩ ድክመቶችን በተግባር ማሻሻል ላይ እንዲተኮር አቅጣጫ አስቀምጠዋል።
የቢሮው መ/ኮሚኒኬሽን
የ 2018 ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ በሠላም እንዲጠናቀቅ ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ የማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል ፍትህ ቢሮ አስታወቀ።
የ 2018 ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ በሠላም እንዲጠናቀቅ
ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ የማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል ፍትህ ቢሮ አስታወቀ።
መጋቢት:-15 /2018 ዓ.ም
የክልሉ ፍትህ ቢሮ በምርጫ ህግ ፤ በጥላቻ ንግግር እና ሀሰተኛ መረጃ ስርጭትን በመከላከል ዙሪያ ያተኮረ የምክክር መድረክ በቡታጀራ ከተማ አካሂዷል።
በመርሀ ግብሩም ከዞንና ከልዩ ወረዳ ፍርድ ቤቶች የተውጣጡ ዳኞች፣ ከፍትሕ መምሪያዎች የተወከሉ ዓቃቢያነ ሕግ፣ ከፖሊስ መምሪያዎች የተገኙ መርማሪ ፖሊሶች እና የሲቪክ ማኅበራት ተወካዮች ተሳትፈዋል።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፍትህ ቢሮ የዐቃቢያነ -ህግ የሙያ ሥነ-ምግባር ረቂቅ መመሪያ ለማሻሻል ከቢሮው ዐቃቢያነ ህጎች ጋር ውይይት አደረገ።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፍትህ ቢሮ የዐቃቢያነ -ህግ የሙያ ሥነ-ምግባር ረቂቅ መመሪያ ለማሻሻል ከቢሮው ዐቃቢያነ ህጎች ጋር ውይይት አደረገ።
ሀላባ መጋቢት 1/2018 ዓ.ም
ቢሮው የ0ቃ ቢያነ - ህግ የሙያ ሥነ - ምግባር ረቂቅ መመሪያን በማዘጋጀት ከቢሮው ዐቃቤ ህጎች ጋር በመወያየት ረቂቁን በተሻለ ለማጎልበት አጋዥ የሚሆኑ ግብዓቶችን ለማግኘት በተደረገው የውይይት መድረክ ላይ ከተወያይዎች ጠቃሚና ገንቢ ሀሳቦች ተሰንዝረዋል። ረቂቁን ባዘጋጁት ቡድኖችም ከቤቱ ለተነሱ ጥያቄዎች እና አስተያየቶች ተገቢውን ምላሽ በመስጠት ረቂቁን በቀጣይ ለማሻሻል ወሳኝ ግብዓቶች ማግኘታቸውን ገልፀዋል።
ለዘገባው የቢሮው መ/ኮ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፍትህ ቢሮ ''ከአኩሪ ታሪከ ፣ ወደ ብሩ አድማስ'' በሚል መሪ ቃል 130ኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት አከበረ።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፍትህ ቢሮ '' ከአኩሪ ታሪከ ፣ ወደ ብሩ አድማስ'' በሚል መሪቃል 130ኛ ውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት አከበረ።
ጥቃትን የማይታገስ ማህበረሰብ ለሀገር ግንባታ" በሚል መሪ ቃል የጸረ ፆታዊ ጥቃት የነጭ ሪቫን ቀን ተከበረ
"ጥቃትን የማይታገስ ማህበረሰብ ለሀገር ግንባታ" በሚል መሪ ቃል የጸረ ፆታዊ ጥቃት የነጭ ሪቫን ቀን ተከበረ
***
ታህሳስ 8/2018
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፍትህ ቢሮ ''
''ጥቃትን የማይታገስ ማህበረሰብ ለሀገር ግንባታ'' በሚል መርህ ቃል በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ34ኛ ግዜ በሀገራችንና በክልላችን ለ20ኛ ጊዜ የሚከበረው የነጭ ሪቫን ቀን በሀላባ ቁሊቶ ከተማ ተከበረ።
በመክፈቻ ንግግር መድረኩን ያስጀመሩት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፍትህ ቢሮ ምክትል ሃላፊ አቶ ኢያሱ ሻንቆ በበኩላቸው የሴቶች ጥቃት በአለም አቀፍ በተለያዩ መልኩ የሚፈጸምና በሰዎች አካል ፣ህይወት እና ንብረት ላይ ጉዳት የሚደርስ ድርጊት መሆኑን ገልፀዋል።
ምክትል ሃላፊ አቶ ኢያሱ ሻንቆ አያይዘውም አካላዊ ፣ስሜታዊ ፣ ሥነልቦናዊ ኢኮኖሚያዊ ማህበራዊ ጉዳት የመብት ጥሰት በማድረስ የሚፈጸም እኩይ ድርጊት መሆኑን ጠቁመ፣
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፍትህ ቢሮ የ 2018 በጀት አመት 1ኛ ሩብ አመት ዕቅድ አፈፃፀም ገመገመ።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፍትህ ቢሮ የ 2018 በጀት አመት 1ኛ ሩብ አመት ዕቅድ አፈፃፀም ገመገመ።
(ሀላባ፣ ጥቅምት 8/ 2018 )
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፍትህ ቢሮ ከተጠሪ ተቋማት ፣ ከዞን ፍትህ መምሪያ እና ከልዩ ወረዳ ፍትህ ጽ/ቤት ጋር የበጀት አመቱን 1ኛ ሩብ አመት ዕቅድ አፈፃፀም በሀላባ ቁሊቶ ከተማ ገምግሟል።
በመድረኩ የቢሮው ኃላፊ አቶ አክመል አህመዲን፣ የዜጎች ሰብዓዊ መብት እንዲከበር፣ ወንጀልን በመከላከል፣ የህግ የበላይነት እንዲረጋገጥ እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል።
በማከልም በፍትህ ተቋማት አሰራርን ከማዘመን አንፃር የሚስተዋሉ ጉድለቶችን ለመቅረፍ እየተሰራ መሆኑን የጠቆሙት የቢሮ ኃላፊው የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመቅረፍ የህዝብ እርካታን ከፍ ለማድረግ መሥራት እንደሚገባ ጠቅሰዋል።
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህግ የበላይነት እንዲረጋገጥ የተሰራው ቅንጅታዊ ስራ ትምህርት ሊወሰድበት የሚችል እንደሆነ ተገለጸ።
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህግ የበላይነት እንዲረጋገጥ የተሰራው ቅንጅታዊ ስራ ትምህርት ሊወሰድበት የሚችል እንደሆነ ተገለጸ።
ጳጉሜ 3/2017 ዓ.ም
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፍትህ ቢሮ የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም እና የ2018 ዓ/ም ዕቅድ የሚመክር ጉባኤ በቡታጅራ ከተማ እያካሄደ ይገኛል።
ጉባኤው “የህግ የበላይነትና ሰብዓዊ ክብር ያረጋገጠ የፍትህ ስርዓት እንገነባለን!” በሚል መሪ ቃል ነው ከሴክተሩ አመራር፣ ከባለድርሻ አካላት እና ከህዝብ ክንፍ አባላት እየተካሄደ የሚገኘው።
አቶ አክመል አህመዲን የክልሉ ፍትህ ቢሮ ኃላፊ ባሰሙት የመክፈቻ ንግግር የተጠናከረ ድጋፍና ክትትል በመደረጉ በሴክተሩ በተሰሩ ስራዎች ላይ ከፍ ያለ ውጤት እንዲመዘገብ ማስቻሉን ገልጸዋል።
የገዢ ትርክትን ቀጣይነት ባለው መልኩ በማስረጽና አንድነትን በማጠናከር የውስጥና የውጭ ፈተናዎችን መሻገር እንደሚገባ ተገለጸ።
የገዢ ትርክትን ቀጣይነት ባለው መልኩ በማስረጽና አንድነትን በማጠናከር የውስጥና የውጭ ፈተናዎችን መሻገር እንደሚገባ ተገለጸ።
ሀላባ: ጳጉሜ/1/2017
ጳጉሜ-1 የጽናት ቀን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሀላባ በቁሊቶ ከተማ በድምቀት ተከብሯል።
ቀኑን በክላስተሩ የሚገኙ የክልል፣ የዞን፣ የቁሊቶ ከተማ አስተዳደርና የዌራ ወረዳ የመንግስት ተቋማት ኃላፊዎች እና ሰራተኞች እንዲሁም የከተማው ማህበረሰብ በጋራ አክብረውታል።
ቀኑን አስመልክቶ ንግግር ያደረጉት የክልሉ ፍትህ ቢሮ ኃላፊ አቶ አክመል አህመዲን የጷጎሜ ቀናትን አከባበር አላማ አስረድተው፤ የዘንድሮውን የጷጎሜ ቀናት አከባበርን ልዩ የሚያደርገው ታላቁን የህዳሴ ግድብ አጠናቀን በምንመርቅበት ወቅት መሆኑ ነው ብለዋል።
በዕለቱ ልዩ ልዩ ወታደራዊ ትርኢት የቀረበ ሲሆን "ጽኑ መሠረት ብርቱ ሀገር" በሚል መሪ ቃል የፓናል ውይይት መነሻ ሰነድ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።