በመስቃንና ማረቆ በአካባቢው የተገኘው አንፃራዊ ሰላም ወደ ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እየተሰሩ ያሉ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ገለፀ።
በመስቃንና ማረቆ በአካባቢው የተገኘው አንፃራዊ ሰላም ወደ ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እየተሰሩ ያሉ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ገለፀ።
ነሀሴ 08/2017ዓ.ም ቢሮው በመስቃንና ማረቆ አካባቢ እስካሁን ያለው የሰላምና ፀጥታ ሁኔታ አስመልክቶ የክልል ፣የዞንና ልዩ ወረዳው የፀጥታ መዋቅሮችና ኮማንድ ፖስት ጋር በቡታጅራ ከተማ ገምግሟል።
ባለፉት ጊዜያት የተሰሩ ሰላምን የማፅናት ተግባራት ቀጣይም ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ተጠናክሮ መስራት እንደሚገባ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምናፀጥታ ቢሮና የክልሉ ፍትህ ቢሮ ከባለድርሻ አካላት ጋር በገመገመበት ወቅት ገልጿል።
የማዕከላዊ ኢትዮያጵያ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተመስገን ካሳ እንደገለፁት በአካባቢው የተገኘው አንፃራዊ ሰላም ወደ ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እየተሰሩ ያሉ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንደሚገባ ገልፀዋል።
የማዕከላዊ ኢትዮያጵያ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ በመስቃንና ማረቆ አካባቢ እስካሁን ያለው የሰላምና ፀጥታ ሁኔታ በቡታጅራ ከተማ እየገመገመ ነው
የማዕከላዊ ኢትዮያጵያ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ በመስቃንና ማረቆ አካባቢ እስካሁን ያለው የሰላምና ፀጥታ ሁኔታ በቡታጅራ ከተማ እየገመገመ ነው
ነሀሴ 8/2017 የማዕከላዊ ኢትዮያጵያ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ በመስቃንና ማረቆ አካባቢ እስካሁን ያለው የሰላምና ፀጥታ ሁኔታ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቡታጅራ ከተማ እየገመገመ ይገኛል።
በመድረኩ የማዕከላዊ ኢትዮያጵያ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ሀላፊና የክልሉ ኮማንድ ፖስት ሰብሳቢ አቶ ተመስገን ካሳ እና ሌሎች የሚመለከታቸው አመራሮች ተገኝተዋል።
ምንጭ :- የክልሉ መ/ኮ
የቱሪዝም ዘርፍ የገቢ ምንጭ ከመሆኑም ባለፈ ለበርካታ ወጣቶች የስራ ዕድል የሚፈጥር መሆኑን የክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ገለፀ
የቱሪዝም ዘርፍ የገቢ ምንጭ ከመሆኑም ባለፈ ለበርካታ ወጣቶች የስራ ዕድል የሚፈጥር መሆኑን የክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ገለፀ
(ነሐሴ 8/2017) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ከቱሪዝም ሚኒስቴር ጋር በመተባበር የተዘጋጀው የስልጢ_ቡታጅራ ጂኦ ፓርክ ክልላዊ ማስጀመሪያ መድረክ በወራቤ ከተማ እየተካሄደ ነው።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ሀላፊ አቶ ሳሙኤል መንገሻ እንደተናገሩት እንደ ክልል በቱሪዝም ዘርፍ በርካታ ስራዎች እየተሰሩ ቢሆንም ከዘርፉ ማግኘት ያለበትን ጥቅም ማግኘት እንዳልተቻለ ገልፀዋል።
በክልሉ 11 የቱሪስት መስህቦችን ለማልማት ፕሮጀከት ተቀርጾ ወደ ስራ መገባቱን በመግለጽ መስህቦች ለምቶ አገልግሎት መስጠት ሲጀምር የገቢ ምንጭ ከመሆኑም ባለፈ ለበርካታ ወጣቶች የስራ ዕድል የሚፈጥር ነው ብለዋል።
ከቱሪዝም ሚኒስቴር ጋር በመተባበር የተዘጋጀው የጂኦ ፓርክ የምክክር መድረክ ለቀጣይ ዘርፉን የበለጠ ለማሳደግ የሚረዳ እንደሆነም ተናግረዋል።
የከተማ ምግብ ዋስትናና ስራ ፕሮጀክት የ2017 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ማጠቃለያ እና የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ ማናበብ መርሃ-ግብር በዛሬው ዕለት በቡታጅራ ከተማ ተጀምሯል።
የከተማ ምግብ ዋስትናና ስራ ፕሮጀክት የ2017 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ማጠቃለያ እና የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ ማናበብ መርሃ-ግብር በዛሬው ዕለት በቡታጅራ ከተማ ተጀምሯል።
(ነሐሴ 8/2017 ) በፌዴራል መንግስትና በዓለም ባንክ ድጋፍ በተመረጡ ከተሞች ለመተግበር በተመደበው በጀት በክልሉ ልዩ ልዩ ፕሮጀክቶችን በማከናወንና ተጠቃሚዎችን ከተረጅነት ወደ አምራችነት ለማሸጋገር በ2017 በጀት ዓመት የተጀመረውና የተከናወኑ የከተሞች ልማታዊ ሴፍቲኔት ስራዎች ላይ የክልሉ ስትሪንግ ኮሚቴ አባላት እየገመገመ ነው።
በምክትል ርዕሰ መስተደድር ማዕረግ የከተማ ልማትና ኢንዱስትሪ ክላስተር አስተባባሪና የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ስንታየሁ ወልደሚካኤል የመድረኩ ዓላማ በከተማ ምግብ ዋስትናና ስራ ፕሮጀክት የተከናወኑ የ2017 በጀት ዓመት ስራዎች አፈጻጸም መገምገምና የ2018 በጀት ዓመት ዋና ዋና ዕቅዶች ላይ መናበብና የጋራ ማድረግ ነው ብለዋል።
የኢቢሲ ዲጂታል አሠራር እና የይዘት ስብጥር ለሌሎችም ሚዲያዎች አዲሱን ምዕራፍ የከፈተ ነው - ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር)
የኢቢሲ ዲጂታል አሠራር እና የይዘት ስብጥር ለሌሎችም ሚዲያዎች አዲሱን ምዕራፍ የከፈተ ነው - ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር)
(ሆሳዕና፣ ነሃሴ 7/2017)፣ የኢቢሲ ዲጂታል አሠራር እና የይዘት ስብጥር የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም የሚያስጠብቅ እና ለሌሎችም ሚዲያዎች አዲሱን ምዕራፍ የከፈተ መሆኑን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር እና የኢቢሲ ቦርድ ሰብሳቢ ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) ተናገሩ።
መረጃ የሰዎችን የዕለት ከዕለት ኑሮ በብዙ መልኩ በሚዳስስበት በዚህ ጊዜ፣ ኢቢሲ መረጃን በተለያዩ አማራጮች የሁሉንም መልክ በሚያሳይ መልኩ ተደራሽ ማድረጉ ለኢትዮጵያ ሚዲያ አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት መሆኑንም አንሥተዋል።
በማኅበራዊ ሚዲያ መረጃ በሰከንዶች ልዩነት ዓለምን በሚያካልልበት በዚህ ጊዜ የተዛቡ ትርከቶችን የሚያስተላልፉ በርካቶች እንዳሉም ሚኒስትሩ አንሥተዋል።
በክልሉ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ16 ነጥብ 9 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ መቻሉ ተጠቆመ
በክልሉ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ16 ነጥብ 9 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ መቻሉ ተጠቆመ
(ሆሳዕና፣ነሐሴ 7/2017)በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ቢሮ የ2017 በጀት ዓመት ፋይናንሻል እና ፊዚካል ስራዎች አፈጻጸም ፣የክረምት ስራዎች ገቢ አሰባሰብ ለመገምገም እና በ2018 በጀት ዓመት እቅድ ላይ የጋራ መግባባት መፍጠር የሚያስችል የምክክር መድረክ በወራቤ ከተማ እየተካሔደ ነው
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ደግፌ መለሰ እንደገለጹት ክልሉ የሚያመነጨውን ኢኮኖሚ በተገቢው መንገድ ለመሰብሰብ ዘርፈ ብዙ ስራ ተግባራዊ ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል።
20 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር ገቢ ለመሰብሰብ መታቀዱን የገለጹት አቶ ደግፌ በበጀት ዓመቱ ከ16 ነጥብ 9 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ ስለመሰብሰቡ አስረድተዋል።
እንደ ምክትል ኃላፊው ገለጻ በክልሉ ከሌሎች አመታት በተለየ መልኩ ከፍ ያለ ገቢ ለመሰብሰብ የታቀደበት ዓመት እንደነበር አስታውሰዋል።
የፍትሕ ሚኒስቴር የአስተዳደር ፍትሕ ላይ የሚደረጉ ትብብሮችን አስመለክቶ ከጂ አይ ዜድ (GIZ) ተወካዮች ጋር ዉይይት አካሄደ
የፍትሕ ሚኒስቴር የአስተዳደር ፍትሕ ላይ የሚደረጉ ትብብሮችን አስመለክቶ ከጂ አይ ዜድ (GIZ) ተወካዮች ጋር ዉይይት አካሄደ
******************
የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ፍትሕ ሚኒስቴር የህግና ፍትሕ አገልግሎት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ በላይሁን ይርጋ እና የተቋም ግንባታ የሪፎርም ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ኤርሚያስ የማነብርሀን (ዶ/ር) ከጀርመን የልማት ተራድኦ ድርጅት (ጂ.አይ.ዜድ) ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ጋር የአስተዳደር ፍትሕ ላይ የሚደረጉ ትብብሮች እና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮችን አንስተዉ ተወያይተዋል፡፡
በውይይታቸውም ኢትዮጵያና ጀርመን የፌዴራል መንግስት አወቃቀርን የሚከተሉ አገራት እንደመሆናቸዉ መጠን የሚከተሏቸዉ ስርዓቶችም በዛዉ ልክ ተመሳሳይነት ያላቸዉ መሆናቸዉ የተገለፀ ሲሆን ከዚህ አንጻር የአስተዳደር ስነ-ስርዓት ህግ ማርቀቅ ጋር በተያያዘ ከዚህ በፊት ከጀርመን ልምድ የተወሰደ መሆኑን፣ ይህም በተለይ ክልሎች ይህን ህግ በሚያወጡበት ወቅት ትልቅ እገዛ እንዳደረገ ተነስቷል፡፡
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የሚወግነው ለሀገር ብቻ ነው - ፕሮፌሰር መስፍን ዓርዓያ
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የሚወግነው ለሀገር ብቻ ነው - ፕሮፌሰር መስፍን ዓርዓያ
(ነሃሴ 6/2017)፣ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የሚወግነው ለሀገር እና ለሕገ-መንግስት ብቻ መሆኑን፤ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽር ፕሮፌሰር መስፍን ዓርዓያ ገለጹ።
ዋና ኮሚሽነሩ አክለውም ከሁሉም ሰው የተሰበሰቡ ሃሳቦች በጋራ ተነጥረው በወጡት ላይ እንመክራለንም ነው ያሉት።
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በትግራይ ክልል እና በዳያስፖራው ማኅበረሰብ አካባቢ አጀንዳ ለመሰብሰብ እየተደረጉ ያሉ እንቅስቃሴዎችን በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥቷል።
ማብራሪያውን የሰጡት የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን ዓርዓያ እንደገለፁት፤ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ወደ በትግራይ ክልል ሥራዎቹን ለማከናወን ዝግጅቱን በመጨረስ ላይ ይገኛል።
ከዳያስፖራው ማኅበረሰብ ጋርም የምክክር ሥራዎች መጀመራጀውን አንስተው፤ በውጭ ሀገራት የሚደረገው ምክክርም እንደሚቀጥል ተናግረዋል።
በአፍሪካ ትልቁ ዓለምአቀፍ የአውሮፕላን ማረፊያ በቢሾፍቱ
በአፍሪካ ትልቁ ዓለምአቀፍ የአውሮፕላን ማረፊያ በቢሾፍቱ
ከ75 ዓመታት በላይ አፍሪካን ከዓለም ያገናኘው የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሚጠቀምበት የቦሌ ዓለምአቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ደንበኞችን የማስተናገድ አቅሙ በዓመት እስከ 25 ሚሊዮን የደረሰ ቢሆንም፤ እያደገ ያለውን የአቪየሽን ፍላጎት ማሟላት አልተቻለም።
ይህን ፍላጎት ለማሟላትም ከአዲስ አበባ 40 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ፤ በ10 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር የቢሾፍቱ ዓለምአቀፍ የአውሮፕላን ማረፊያን ለመገንባት እንቅስቃሴ ተጀምሯል።
አዲሱን የአውሮፕላን ማረፊያ መገንባት እያደገ ያለውን የአቪዬሽን ዘርፍ ፍላጎት ለሟሟላት፣ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ለማሳደግ እና ሀገሪቱ በአቪየሽን ዘርፍ መሪነቷን አጠናክራ እንድትቀጥል ያስችላል ብለዋል የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ።
የጤና አገልግሎት ጥራትን ለማሻሻል እየተሰሩ የሚገኙ ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ - ዶ/ር መቅደስ ዳባ
የጤና አገልግሎት ጥራትን ለማሻሻል እየተሰሩ የሚገኙ ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ - ዶ/ር መቅደስ ዳባ
( ነሐሴ 6፣ 2017) የአገልግሎት ጥራትን ለማሻሻል እየተሰሩ የሚገኙ ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ አሉ የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ።
የሚኒስቴሩና የክልል ጤና ቢሮ ከፍተኛ አመራሮች የጋራ ምክክር መድረክ በሀረር ከተማ እየተካሄደ ነው።
በመድረኩ የጤና ሚኒስትሯ ዶ/ር መቅደስ ዳባ በተጠናቀቀው የ2017 የበጀት ዓመት በጤናው ዘርፍ አበረታች ስራዎች መከናወናቸውን አንስተው÷ የጤና አገልግሎት ጥራትን በማሻሻል ረገድ እየተሰሩ የሚገኙ ተግባራትን ለማጠናከር ትኩረት ይሰጣል ብለዋል።
እንደ ኤፍ ኤም ሲ ዘገባ በቴክኖሎጂ የተደገፉ ስራዎች እውን በማድረግና በቅንጅት በመስራት የተገኙ ውጤቶችን ለማጎልበትና የታዩ ውስንነቶች ለመቅረፍ መረባረብ እንደሚገባም ተናግረዋል።