Skip to main content

በሞባይል ባንኪንግ ማጭበርበር ወንጀል በተጠረጠሩ 20 ግለሰቦች ላይ ክስ ተመሰረተ

በሞባይል ባንኪንግ ማጭበርበር ወንጀል በተጠረጠሩ 20 ግለሰቦች ላይ ክስ ተመሰረተ

ሆሳዕና፣ሐምሌ 7/2017)በሞባይል ባንኪንግ ማጭበርበር ወንጀል በተጠረጠሩ 20 ግለሰቦች ላይ የፌደራል ዐቃቤ ሕግ ክስ እንደመሰረተ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ተገልጿል።

ይህ የተገለጸው የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የ2016/2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀምን ከተለያዩ የዘርፉ ተጠሪዎች ጋር እየገመገመ ባለበት መድረክ ላይ ነው።

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ ተወካይ አቶ ሙሊሳ አብዲሳ ባቀረቡት ሪፖርት፣ በሞባይል ባንኪንግ አማካኝነት ከ116 ግለሰቦች ላይ ከ30 ሚሊዮን ብር በላይ በሞባይል ባንኪግ በማጭበርበር ወንጀል በተጠረጠሩ 20 ግለሰቦች ላይ የፌደራል ዐቃቤ ሕግ ክስ እንደተመሰረተባቸውገልጸዋል።

አመራር አካዳሚው በጥናትና ምርምር ዘርፈ ብዙ ስራዎች መሰራቱን የክልሉ ምክር ቤት ማህበራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አስታወቀ።

አመራር አካዳሚው በጥናትና ምርምር ዘርፈ ብዙ ስራዎች መሰራቱን የክልሉ  ምክር ቤት ማህበራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አስታወቀ።

(ሆሳዕና፦ሀምሌ 8/2017) ቋሚ ኮሚቴው የክልሉ አመራር አካዳሚ  2017 በጀት ዓመት የተከናወኑ ተግባራትን ገምግሟል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የማህበራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ  አቶ ግዛቸው ዋሌራ እንዳሉት በአካዳሚው በጥናትና ምርምር ዘርፈ ብዙ ስራዎች መሰራቱን ገልፀዋል።

አካዳሚው ለተለያዩ አስፈጻሚዎችና ፈጻሚዎች የአቅም ግንባታ እየሰጠ ያለበት አግባብ የሚያበረታታ ነው ብለው  በጥናትና ምርምር ዘርፍ በበጀት ዓመቱ የተሰሩ ስራዎች አበረታች ቢሆንም ጥናቱ የህብረተሰቡን ችግር የሚፈታና ተጠቃሚ የሚያደርጉ ሊሆኑ ይገባል ነው ያሉት።

አካዳሚው እስከታችኛው መዋቅር ድረስ ክፍተቶችን በመለየት እየሰጠ ያለው የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች  ተጨባጭ ለወጥ አምጥቶ የህዝብ ተጠቃሚነት እስከሚረጋገጥ በትኩረት ሊሰራ ይገባል ብለዋል።

በክልሉ ላቦራቶሪን በማደራጀት በማስመረቅ የምርመራ አገልግሎቶችን በማስጀመርና በማጠናከር ረገድም የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ከፍተኛ ውጤት ማስመዝገቡ ተመላከተ።

በክልሉ ላቦራቶሪን በማደራጀት በማስመረቅ የምርመራ አገልግሎቶችን በማስጀመርና በማጠናከር ረገድም የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ከፍተኛ ውጤት ማስመዝገቡ ተመላከተ።

ሆሳዕና ሐምሌ 08/2017 ዓ.ም

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የ2017 ዓ.ም ዓመታዊ አፈጻጸም እና የ2018 በጀት አመት የትኩረት አቅጣጫዎች የውይይት መድረክ በወራቤ ከተማ እየተካሄደ ነው።

የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ሳሙኤል ዳርጌ በመድረኩ ባስተላለፉት መልዕክት እንድ ክልል አምስት ግቦችን በማስቀመጥ ወደ ስራ መገመቱን ጠቅሰው ሁሉ አቀፍ የጤና አገልግሎት ሽፍን ማፍጠን በሚያስችል መልኩ በርካታ ስራ መሰራቱን ገልጸዋል።

ከጤና ተቋማት ተደራሽነት አገልግሎት አቅርቦት ፍትሀዊ የጤና አገልግሎት ለህብረተሰቡ ከማድረስ፣የህብረተሰብን የጤና ሁኔታን ማሻሻል ጥራት ፍትሀዊነት ተደራሽነትን ታሳቢ ያደረገ፣ህብረተሰቡን ከድንገተኛ አደጋዎች የመጠበቅ ስራዎችን ቢሮው በትኩረት መስራቱን ኃላፊው አስታውቀዋል።

የክልሉ ግብርና ቢሮ የተሻሻሉ ቴክኖሎጂ እና የግብርና ግብአቶችን በአግባቡ በመጠቀም ህብረተሰቡን ተጠቃሚ እንዲሆን ማስቻሉ ተገለፀ።

የክልሉ ግብርና ቢሮ የተሻሻሉ ቴክኖሎጂ እና የግብርና ግብአቶችን በአግባቡ በመጠቀም ህብረተሰቡን ተጠቃሚ እንዲሆን ማስቻሉ ተገለፀ።

(ሆሳዕና፦ሀምሌ 7/2017)፣ የክልሉ ምክር ቤት የግብርናና ገጠር ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የግብርናን ቢሮ የ2017 በጀት ዓመት የስራ አፈጻጸም ገምግሟል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርናና ገጠር ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ  ወ/ሮ ልክነሽ ስርገማ እንዳሉት የአርሶአደሩን ምርትና ምርታማነትን በማሳደግና ተጠቃሚ በማድረግ ረገድ በግብርና ቢሮ የተሰሩ ስራዎች አበረታች ነው ብለዋል።

የክልሉ ግብርና ቢሮ የተሻሻሉ ቴክኖሎጂ እና የግብርና ግብአቶችን በአግባቡ በመጠቀም ህብረተሰቡን ተጠቃሚ እንዲሆን ማስቻሉን በግምገማው አንስተው ገበያ ተኮር የአመራረት ዘዴን በመከተል ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ በተደረገው ርብርብ ተጫባጭ ለውጦችን ማስመዝገብ ተችሏል።

ሙስናን በቅንጅት በመከላከል የህግ የበላይነት እንዲሰፍን በልዩ ትኩረት ሊሰራ እንደሚገባ የክልሉ ምክር ቤት የህግና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ገለፀ

ሙስናን በቅንጅት በመከላከል የህግ የበላይነት እንዲሰፍን በልዩ ትኩረት ሊሰራ እንደሚገባ የክልሉ ምክር ቤት የህግና አስተዳደራዊ ጉዳዮች  ቋሚ ኮሚቴ ገለፀ

(ሆሳዕና፦ ሀምሌ 8/2017) ቋሚ ኮሚቴው  የክልሉን ስነ-ምግባርና ፀረ- ሙስና ኮሚሽን የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸምን ገምግሟል።

የክልሉ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የህግና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ   ወ/ሮ መሰረት ወ/ሰንበት እንዳሉት ሙስናን በቅንጅት በመከላከል  የህግ የበላይነት  እንዲሰፍን አበክሮ ሊሰራ ይገባል።

በፀረ ሙስነ ትግል ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት ለመስራት የተካሄደበት አግባብ ጥሩ ሆኖ ሙስናን በመከላከልና ሙስናን የሚጸየፍ ዜጋን ለማፍራት ሌተ ቀን መስራት ያስፈልጋል ብለዋል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የአስፈጻሚ አካላት የበጀት ዓመቱን ዕቅድ አፈጻጸም እየገመገመ ነው።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር  ቤት የአስፈጻሚ አካላት የበጀት ዓመቱን ዕቅድ አፈጻጸም እየገመገመ ነው።

(ሆሳዕና፦ሀምሌ 7/2017) በምክር ቤቱ ፕላን መሰረተ ልማትና የመንግስት ሀብት ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የክልሉን ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ የበጀት ዓመቱን ዕቅድ አፈጻጸምን በወልቂጤ ከተማ ገምግሟል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ፕላን መሰረተ ልማትና የመንግስት ሀብት ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ  አቶ ታመነ ገብሬ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ህብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ በርካታ ስራዎች ተሰርቷል ብለዋል።

ቢሮው በበጀት ዓመቱ ያከናወናቸው ሰው ተኮር ተግባራት የሚያበረታታ እንደሆነም ገልፀዋል።

የህብረተሰቡን ኑሮ ውድነትን ለመቀነስ የተጀመረው የሰንበት ገበያ ስራን በማጠናከር አቅራቢውን እና ሸማቹን ማህበረሰብ ተጠቃሚ እያደረገ በመሆኑ ለጥራቱ  በልዩ ትኩረት ተሰጥቶ ሊሰራ ይገባል ነው ያሉት።

በክልሉ የህዝብ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ በሚያስችሉ ተግባራት ላይ በትኩረት መስራት ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻዉ ጣሰዉ (ዶ/ር)

በክልሉ  የህዝብ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ በሚያስችሉ ተግባራት ላይ በትኩረት መስራት ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻዉ ጣሰዉ (ዶ/ር)

(ሆሳዕና፣ሐምሌ 7/2017)የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻዉ ጣሰዉ (ዶ/ር )ከዞኖችና ከልዩ ወረዳ አመራሮች ጋር በጽ/ቤታቸው እየመከሩ ነው

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻዉ ጣሰዉ (ዶ/ር በምክክር መድረኩ እንደገለጹት የክልሉን መንግስት የ2017 በጀት አመት አፈጻጸም አስመልክቶ በቀረበው ሪፖርት ላይ ውይይት ይካሔዳል ብለዋል።

በክልሉ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገር የተከናወኑ  ስራዎች ሪፖርት፣የፋይዳ ብሔራዊ መታወቂያ፣የ5 ሚሊየን ኮደርስ፣የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች ቀን በአል አከባበር የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እና በሌሎችም አጀንዳዎች ላይ የጋራ መግባባት መፍጠር የሚያስችል መድረክ ስለመሆኑም ርዕሰ መስተዳድሩ አብራርተዋል።

የሴቶችና ህፃናትን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በቅንጅት መስራት ያስፋልጋል - ወ/ሮ ሂክማ ከይረዲን

የሴቶችና ህፃናትን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በቅንጅት መስራት ያስፋልጋል -  ወ/ሮ ሂክማ ከይረዲን

የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር አመራሮች እና ባለሙያዎች በክልሉ በሴቶችና ህጻናት ዘርፍ የተከናወኑ ተግባራትን ምልከታ አድርገዋል።

(ሆሳዕና፦ ሀምሌ 6/2017) ፣ የኢፌዴሪ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር አመራሮችና ባለሙያዎች ቡድን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጉራጌ ዞን በሴቶችና ህፃናት ዘርፍ የተሰሩ ተግባራትን ነው ምልከታ ያደረገው።

የኢፌዴሪ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር  ሴቶችና ህፃናት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሂክማ ከይረዲን እንደተናገሩት ከድህነት ለመላቀቅ በሴቶች ህብረት መደራጀት የሴቶችን ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ተጠቃሚነት እያሳደገ ነው ብለዋል።

ሴቶች የኢትዮጵያን ብልጽግና የሚያረጋግጡ  ናቸው ያሉት ወ/ሮ ሂክማ የሴቶችንና ህፃናትን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ በቅንጅት መስራት ያስፈልጋል ሲሉም ተናግረዋል።

በመኸር እርሻ እስካሁን 7 ሚሊየን ሄክታር በዘር ተሸፍኗል::

በመኸር እርሻ እስካሁን 7 ሚሊየን ሄክታር በዘር ተሸፍኗል

ሆሳዕና ፣ ሐምሌ 6፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ2017/18 የመኸር ወቅት እርሻ እስካሁን 7 ሚሊየን ሄክታር መሬት በዘር ተሸፍኗል አሉ የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር)።

ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) እንዳሉት ÷ በግብርናው ዘርፍ በመኸር፣ በበልግ እንዲሁም በመስኖ ልማት ሥራዎች ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ ሥራዎች አመርቂ ውጤት ተመዝግቧል፡፡

በዚህ ዓመት በመላ ሀገሪቱ 21 ሚሊየን ሄክታር መሬት በመኸር እርሻ በተለያዩ ሰብሎች በዘር እንደሚሸፈን ነው የተናገሩት፡፡

አሁን ላይ በከፍተኛ ሁኔታ የዘር ሥራ የሚከናወንበት በመሆኑ እንደ በቆሎ ያሉ የአገዳ ሰብሎች ቀድሞ መዘራታችን ጠቁመው÷ ጤፍ፣ ስንዴ፣ ገብስና ሌሎች እንደየ አካባቢው ሥነ ምህዳር እየተዘሩ ነው ብለዋል፡፡

ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም እና ለአርሶ አደሩ ግንዛቤ በመፍጠር ጭምር በመሰራቱ በዚህ ዓመት የተሻለ ምርት ይጠበቃል ነው ያሉት፡፡

የምስራቅ ጉራጌ  ዞን የ2017 ዞናዊ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በሶዶ ወረዳ ጢያ ከተማ "በመትከል ማንሰራራት"  በሚል መሪ  ቃል የችግኝ ተከላ  እየተካሄደ ነው::

የምስራቅ ጉራጌ  ዞን የ2017 ዞናዊ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በሶዶ ወረዳ ጢያ ከተማ "በመትከል ማንሰራራት"  በሚል መሪ  ቃል የችግኝ ተከላ  እየተካሄደ ነው።

(ሆሳዕና፣ሐምሌ 06/2017)፣ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የገጠር ልማት ክላስተር አስተባባሪ እና የክልሉ ግብርና  ቢሮ ኃላፊ አቶ ኡስማን ሱሩርና የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙስጠፋ ሀሰን ዞናዊ የአረንጓዴ አሻራ ፕሮግራም በሶዶ ወረዳ ጢያ ከተማ አስጀምረዋል።በዕለቱ ለምግብነት የሚውሉ አትክልትና ፍራፍሬዎች በመትከል አሻራቸውን አኑረዋል።በዘንድሮው ዓመት በዞኑ ከሀያ አምስት ሚሊየን ችግኝ ሁሉም የማህበረሰብ ክፍሎች በማሳተፍ  የተለያዩ ጠቀሜታ ያላቸው  ፍራፍሬና አትክልቶች እንደሚተከሉ ተጠቅሷል።በመረሃ ግብሩ የዞኑ፣የወረዳውና የከተማ አስተዳደር አመራሮችና ነዋሪዎች አሻራቸውን ማኖራቸውን ከዞኑ የመንግስት ኮሙኒኬሽን መምሪያ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።


ምንጭ :- የክልሉ መ/ኮ