Skip to main content

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በ3ኛ ቀን ውሎው በ2018 በጀት ዓመት እቅድ ላይ እየመከረ ነው::

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በ3ኛ ቀን ውሎው በ2018 በጀት ዓመት እቅድ ላይ እየመከረ ነው::

(ሆሳዕና፣ሐምሌ 4/2017)የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በ29ኛ መደበኛ ስብሰባው በ2018 በጀት ዓመት እቅድ ላይ እየመከረ ነው

መስተዳድር ምክር ቤቱ በ3ኛ ቀን ውሎው በልዩ ልዩ አጀንዳዎች ላይ በመምከር አቅጣጫ ያስቀምጣል ተብሎ ይጠበቃል።

ምንጭ የክልሉ መ/ኮ

ባሳለፍነው አመት የክልሉን ጸጥታ በማስከበር የህዝቡ ሰላም እንዲጠበቅና የክልሉ የልማት እንቅስቃሴዎች እንዳይስተጓጎሉ ለማድረግ የተሰሩ ፖሊሳዊ ስራዎች ውጤታማ እንደነበሩ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ገለጸ።

ባሳለፍነው አመት የክልሉን ጸጥታ በማስከበር የህዝቡ ሰላም እንዲጠበቅና የክልሉ የልማት እንቅስቃሴዎች እንዳይስተጓጎሉ ለማድረግ የተሰሩ ፖሊሳዊ ስራዎች ውጤታማ እንደነበሩ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ገለጸ።

በቀጣዩ አመት በክልሉ አዘጋጅነት ለሚካሄደው የብሄር ብሄረሰቦች በኣልና ሀገራዊ ምርጫ ከወዲሁ የተሟላ ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የፖሊስ ኮሚሽኑ አስታውቋል ።  

በተጠናቀቀው በጀት አመት የክልሉን ጸጥታ በማስከበር የህዝቡ ሰላም በአስተማማኝ ሁኔታ እንዲጠበቅና የክልሉ የልማት እንቅስቃሴዎች እንዳይስተጓጎሉ ለማድረግ የተሰሩ ቅንጅታዊ የፖሊስ ተግባራት ውጤታማ እንደነበሩ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ገልጿል።

ኮሚሽኑ የ2017 በጀት አመት አፈጻጸሙን የዞንና ልዩ ወረዳ የፖሊስ አመራሮች በተገኙበት በሆሳዕና የገመገመ ሲሆን በዚሁ ወቅት እንዳለው ግጭቶችን አስቀድሞ በመከላከል የክልሉ ሰላምና ጸጥታ አስተማማኝና ዘላቂ እንዲሆን ውጤታማ ተግባራት ተከናውነዋል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሴቶችና ህጻናት ጉዳይ ቢሮ የህጻናትን መብትና ደህንነት ለማስጠበቅ በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ ገለጸ።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሴቶችና ህጻናት ጉዳይ ቢሮ የህጻናትን መብትና ደህንነት ለማስጠበቅ በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ ገለጸ።

(ሃምሌ 3/2017)፣ በተሻሻለው አዲሱ አማራጭ የህጻናት ድጋፍና እንክብካቤ መመሪያ ላይ በየደረጃው ለሚገኙ አመራሮችና ባለሙያዎች በዱራሜ ከተማ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል።

የክልሉ ሴቶችና ህጻናት ጉዳይ ቢሮ ምክትል ኃላፊ እና የህፃናት ዘርፍ ኃላፊ ወይዘሮ አምሪያ ሲራጅ ስልጠናውን በንግግር በከፈቱበት ወቅት ቢሮው የህጻናትን መብትና ደህንነት ለማስጠበቅ በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

በተፈጥሮአዊ እና ሰውሰራሽ አደጋዎች ለተጋለጡ ህጻናት በማህበረሰብ አቀፍ ድጋፍና ክብካቤ የተለያዩ ድጋፎች ሲደረጉ መቆየታቸውን ኃላፊዋ ተናግረዋል።

ወይዘሮ አምሪያ ባልተደራጀ መንገድ ሲሰጥ የነበረውን ድጋፍ እና እንክብካቤ የተደራጀና ዘላቂ መፍትሄ በሚያመጣ መልኩ መፈጸም ማስቻል የስልጠናው አላማ መሆኑን ተናግረዋል።

መስተዳድር ምክር ቤቱ በሁለተኛ ቀን ውሎው የክልሉን መንግስት የ2017 ዓ.ም አፈጻጸም አስመልክቶ በቀረበው ሪፖርት ላይ እየመከረ ነው

መስተዳድር ምክር ቤቱ በሁለተኛ ቀን ውሎው የክልሉን መንግስት የ2017 ዓ.ም  አፈጻጸም አስመልክቶ በቀረበው ሪፖርት ላይ እየመከረ ነው

ሆሳዕና፣ ሐምሌ 3/2017 የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መስተዳድር ም/ቤት በሁለተኛ ቀን ውሎው  በክልሉ መንግስት የ 2017 በጀት ዓመት አፈጻጸም አስመልክቶ በቀረበው ሪፖርት ላይ እየመከረ ነው።

መስተዳድር ምክር ቤቱ በ29ኛ መደበኛ ስብሰባው በቀረቡለት ልዩ ልዩ አጀንዳዎች ላይ በመምከር ውሳኔ ያስተላልፋል ተብሎ ይጠበቃል።

ምንጭ ፦ የክልሉ መ/ኮ

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) የ12ኛ ክፍል የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎችን ብሄራዊ ፈተና በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የፈተና ማዕከል አስጀመሩ ።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) የ12ኛ ክፍል የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎችን ብሄራዊ ፈተና በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የፈተና ማዕከል አስጀመሩ ።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ከዛሬ ጀምሮ ባሉት ሶስት ተከታታይ ቀናት የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ብሄራዊ ፈተናን በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የፈተና ማዕከል አስጀምረዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ በዚሁ ወቅት ለተማሪዎቹ መልካም ውጤት ተመኝተዋል።

በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ፣ የክልሉ መንግስት ዋና ተጠሪ ዲላሞ ኦቶሬ(ዶ/ር)፣ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ፣ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ሃላፊ አቶ አንተነህ ፍቃዱ፣  የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ኤርሲኖ አቡሬ እና ሌሎችም ከፍተኛ የክልሉ አመራሮች ተገኝተዋል።

በክልሉ ከ500 ሚሊየን በላይ ችግኞች ለመትከል የቅድመ ዝግጅት ስራ ተጠናቋል - አቶ ኡስማን ሱሩር

በክልሉ ከ500 ሚሊየን በላይ ችግኞች ለመትከል የቅድመ ዝግጅት ስራ ተጠናቋል - አቶ ኡስማን ሱሩር

(ሆሳዕና፣ሰኔ 30/2017)በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ነገ ሀምሌ 1/2017 ክልላዊ የአረንጓዴ አሻራ እና የገጠር ኮሪደር ማስጀመሪያ መርሐ ግብር እንደሚካሔድም ተመላክቷል

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ልማት ክላስተር አስተባባሪ እና የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኡስማን ሱሩር ለመገናኛ ብዙሀን በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት ነገ ሀምሌ1/2017 ክልላዊ የአረንጓዴ አሻራ እና የገጠር ኮሪደር ማስጀመሪያ መርሐ ግብር ይካሄዳል ብለዋል።

በጉራጌ ዞን ጉመር ወረዳ በሚካሄደው ክልላዊ የአረንጓዴ አሻራ ማስጀመሪያ መርሐ ግብር ላይ ከ500 ሚሊየን በላይ ችግኞች እንደሚተከሉም ኃላፊው በመግለጫቸው አመላክተዋል።

በክልሉ ከ310 ሚሊየን በላይ የፎራፍሬ፣የቡና የእንስሳት መኖ እና ሌሎች ከፍተኛ የኢኮኖሚ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች ተከላ እንደሚካሔድ ኃላፊው አብራርተዋል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፍትህ ቢሮ የ 2017 በጀት ዓመት የሁለተኛ መንፈቅ አመት የስር መዋቅር የOቃቤ ህግ የድጋፍ ክትትል ሪፖርት ገመገመ።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፍትህ ቢሮ የ 2017 በጀት ዓመት የሁለተኛ መንፈቅ አመት የስር መዋቅር የOቃቤ ህግ የድጋፍ ክትትል ሪፖርት ገመገመ።

####################

(ሀላባ ፣ ሰኔ 30/ 2017)  የክልሉ ፍትህ ቢሮ ከቢሮው ማኔጅመንት አካላት ጋር የበጀት ዓመቱን የ0ቃቤ ህግ የድጋፍ ክትትል ሪፖርት ግምገማ አካሄደ። ቢሮው የተጣለበትን ተግባርና ኃላፊነት ለመወጣት እና ተልዕኮውን መሠረት ያደረገ የ 7 ዓመት ስትራቴጅክ ዕቅድ በማዘጋጃት  የ2016 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ጥንካሬ እና ድክመት በመገምገም የ 2017 በጀት ዕቅድ ተዘጋጅቶ ባለፉት 12 ወራት ሲተገበር ቆይቷል።

ምክር ቤቱ በልዩ ስብሰባው ውሳኔ የተሰጠበትን ድንጋጌ አርሞ አፀደቀ

ምክር ቤቱ በልዩ ስብሰባው ውሳኔ የተሰጠበትን ድንጋጌ አርሞ አፀደቀ
-------------------
(ዜና ፓርላማ) ሰኔ 30 ፣ 2017 ዓ.ም፤ አዲስ አበባ፤ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 3ኛ ልዩ ስብሰባው፤ በምክር ቤቱ የአሠራር እና የአባላት ሥነ-ምግባር ደንብ ቁጥር 6/2008 አንቀፅ 49 (2)ሀ መሠረት ውሳኔ የተሰጠበት ድንጋጌ እንዲታረም በሚል ከሕግና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የቀረበ የውሳኔ ሃሳብ መርምሮ አፅድቋል፡፡

ምክር ቤቱ በልዩ ስብሰባው፤ ከአሁን በፊት ውሳኔ የተሰጠበት ድንጋጌ እንዲታረም የቀረበለትን ረቂቅ አዋጅ አርሞ አፅድቋል፡፡

ለሰብአዊ መብት ጥሰት በር ይከፍታል የተባለው የአዋጅ ድንጋጌ ተሻሻለ

ለሰብአዊ መብት ጥሰት በር ይከፍታል የተባለው የአዋጅ ድንጋጌ ተሻሻለ

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 3ኛ ልዩ ስብሰባው፤ በምክር ቤቱ የአሠራር እና የአባላት ሥነ-ምግባር ደንብ ቁጥር 6/2008 አንቀፅ 49 (2)ሀ መሠረት ውሳኔ የተሰጠበት ድንጋጌ እንዲታረም በሚል ከሕግና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የቀረበ የውሳኔ ሃሳብ መርምሮ አፅድቋል፡፡

ምክር ቤቱ በልዩ ስብሰባው፤ ከአሁን በፊት ውሳኔ የተሰጠበት ድንጋጌ እንዲታረም የቀረበለትን ረቂቅ አዋጅ አርሞ አፅድቋል፡፡

የሕግና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ የተከበሩ አቶ ኢሳ ቦሩ ሪፖርት እና የውሳኔ ሃሳብ ያቀረቡ ሲሆን፤ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 37ኛ መደበኛ ስብሰባው፤ በወንጀል የተገኘ ንብረት ሕጋዊ ማስመሰል እና ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳት ወንጀልን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር የቀረበ ረቂቅ አዋጅ፤ ረቂቅ አዋጅ ቁጥር 1387/2017 አድርጎ ማፅደቁ አስታውሰዋል፡፡

በ2017 በጀት አመት 16 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰቡን የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ገለጸ።

በ2017 በጀት አመት 16 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰቡን የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ገለጸ።

(ሆሳዕና፣ ሰኔ 30/2017) ፣ የደረጃ ሐ ግብር ከፋዮች ከነገ ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ ቀናት ግብራቸውን እንዲከፍሉ ቢሮው ጥሪ አቅርቧል።

በ2017 በጀት አመት 16 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰቡን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ቢሮ አስታውቋል።

ቢሮው እንዳለው በበጀት አመቱ 20 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር አጠቃላይ ገቢ  ከተለያዩ የገቢ አርእስቶች ለመሰብሰብ ታቅዶ እስከ አሁን ባለው ሂደት 16 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰብ ተችሏል።

የቢሮው ሃላፊ ተወካይና የደንበኞች አገልግሎት የታክስ አወሳሰንና አሰባሰብ ዘርፍ ሃላፊ  አቶ ደግፌ መለሰ በሰጡት መግለጫ እንዳሉት የክልሉ መንግስት ወጪን በሚሰበሰብ ገቢ ለመተካት ባስቀመጠው አቅጣጫ መሰረት የገቢ አማራጮችን ለማስፋት በልዩ ትኩረት እየተሰራ ይገኛል።