Skip to main content

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በወራቤ ከተማ የልማት ፕሮደክቶችን ምልከታ እያደረጉ ነው

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በወራቤ ከተማ የልማት ፕሮደክቶችን ምልከታ እያደረጉ ነው

ሆሳዕና፣ሐምሌ 14/2017)የምክር ቤቱ አባላት በወራቤ ከተማ  የክልል ሴክተር መስሪያ ቤቶች ህንጻ ግንባታ፣ የወራቤ ሶጃት የኢንዱስትሪ መንደር፣የወንዝ ዳር ልማት፣ እና ሌሎች ፕሮጀክቶችን እየተመለከቱ ነው

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ በዚሁ ጊዜ  እንደገለጹት አመራሩ ማህበረሰቡን በማስተባበር በልማት ስራዎች ላይ ከተጋ ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል የወራቤ ኢንዱስትሪ መንደር አመላካች ነው ብለዋል።

የወራቤ ኢንዱስትሪ መንደር ለእርሻ አገልግሎት የማይውል ድንጋያማ አካባቢ መሆኑን የገለጹት ዋና አፈ ጉባኤዋ ይህን ወደ ልማት በመቀየር መሰረታዊ ለውጥ ማምጣት የሚያስችል መሆኑን ጠቁመዋል።

በከተሞች እየተከናወነ ያለው የልማት ስራ የመንግስት ፖሊሲዎች፣ስትራቴጂዎች እና ፕሮግራሞች በተገቢው መንገድ ተፈጻሚ ስለመሆናቸው አመላካች ነው - ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ

በከተሞች እየተከናወነ ያለው የልማት ስራ የመንግስት ፖሊሲዎች፣ስትራቴጂዎች እና ፕሮግራሞች በተገቢው መንገድ ተፈጻሚ ስለመሆናቸው አመላካች ነው - ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ

(ሆሳዕና፣ሐምሌ 14/2017)፣የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በቡታጅራ ከተማ የልማት ፕሮደክቶች ምልከታ አድርገዋል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ እንደገለጹት የመስክ ምልከታው አብይ ዓላማ በበጀት ዓመቱ ለማከናወን የታቀዱ ተግባራት ከወረቀት ሪፖርት ባለፈ ምን ያህል ተፈጻሚ መሆናቸውን ለማረጋገጥ ነው።

በክልሉ የመስክ ምልከታ በተደረገባቸው ከተሞች የመንግስት ፖሊሲዎች፣ስትራቴጂዎች እና ፕሮግራሞች በተገቢው መንገድ ተፈጻሚ ስለመሆናቸው የምክር ቤት አባላት ተገንዝበዋል ሲሉም ዋና አፈ ጉባኤዋ አስረድተዋል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በቡታጅራ ከተማ የልማት ፕሮደክቶችን ምልከታ እያደረጉ ነው

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በቡታጅራ ከተማ የልማት ፕሮደክቶችን ምልከታ እያደረጉ ነው

ሆሳዕና፣ሐምሌ 14/2017)የምክር ቤቱ አባላት በከተማዋ እየተነገባ  ያለውን የኮሪደር ልማት፣የከተማ የውስጥ ለውስጥ አስፋልት መንገድ፣የክልል ተቋማት የግንባታ ፕሮጀክቶች፣የማህበረሰብ አቀፍ መድሀኒት ቤት፣የአረንጓዴ መናፈሻ ስፍራዎችን እና ሌሎች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማሳደግ እየተሰሩ ያሉ የመሰረተ ልማት አውታሮችን እየተመለከቱ ነው

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ በዚሁ ጊዜ  እንደገለጹት በክልሉ መንግስት የተቀረጹት በአንድ ከተማ አንድ ፕሮጀክት የልማት ስራዎች ውጤታማ ናቸው።

በከተሞች እየተገነቡ የሚገኙ ልዩ ልዩ የልማት ስራዎች ፕሮጀክቶችን በጥብቅ ዲሲፕሊን ገንብቶ የማጠናቀቅ ልምድ ማዳበር የተቻለበት ስለመሆኑ ማሳያ ናቸው ብለዋል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባዔ ከሐምሌ 16 እስከ 18 /2017 እንደሚካሄድ ገለፀ

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባዔ  ከሐምሌ 16 እስከ 18 /2017 እንደሚካሄድ ገለፀ

(ሆሳዕና፦ ሀምሌ 11/2017) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ ጉባኤውን በማስመልከት ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።

ከጉባዔው በፊት ቅድመ ጉባዔ በከተማ ሥራዎች ላይ የሁለት ቀናት የመስክ ጉብኝት እንደሚደረግ ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ  ጠቁመዋል።

ጉባዔተኛው ሐምሌ 13/2017 ቡታጅራ ከተማ ገብቶ በማደር ሐምሌ 14 እና 15 በተለያዩ ከተሞች በሚደረጉ የመስክ ጉብኝቶች ላይ እንዲሳተፉ ጥሪ አቅርበዋል።

ከሐምሌ 16 እስከ 18/2017 ድረስ የምክር ቤቱ  6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባዔ   ወልቂጤ ላይ የሚካሄድ መሆኑን በጋዜጣዊ መግለጫቸው ገልፀዋል።

በአባል እና በአመራራችን የጋራ ጥረት ዓመቱን ስኬታማ ያደረጉ ድሎችን መጎናፀፋችንን ገምግመናል፡- አቶ አደም ፋራህ

በአባል እና በአመራራችን የጋራ ጥረት ዓመቱን ስኬታማ ያደረጉ ድሎችን መጎናፀፋችንን ገምግመናል፡- አቶ አደም ፋራህ
(ሆሳዕና ፣ሐምሌ 10/2017)

በአባል እና በአመራራችን የጋራ ጥረት ዓመቱን ስኬታማ ያደረጉ ድሎችን መጎናፀፋችንን ገምግመናል ሲሉ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አደም ፋራህ ተናግረዋል፡፡

ባለፉት ሦስት ቀናት በድሬደዋ ከተማ ሲካሄድ የነበረው የብልፅግና ፓርቲ የ2017 በጀት ዓመት የፓርቲ ስራዎች አፈፃፀም ግምገማ መድረክ ተጠናቋል፡፡

በመድረኩ በበጀት ዓመቱ የተከናወኑ ተግባራት በጥልቅ መገምገማቸውን የገለጹት አቶ አደም፣ኢትዮጵያን ወደ ሁለንተናዊ ብልፅግና ለማሻገር የሚያስችል አቅምን ከጊዜ ወደ ጊዜ እያዳበርን እንደመጣን፣ በአባል እና በአመራራችን የጋራ ጥረት ዓመቱን ስኬታማ ያደረጉ ድሎችን መጎናፀፋችንን ገምግመናል ነው ያሉት።

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የገቢ ግብር ማሻሻያ አዋጅን አጸደቀ

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የገቢ ግብር ማሻሻያ አዋጅን አጸደቀ

(ሆሳዕና፣ሐምሌ 10/2017)የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ የገቢ ግብር ማሻሻያ አዋጅን አፅድቋል።

አዋጁ ከመቀጠር የሚገኝ ገቢ ግብር ነፃ የተደረገውን የብር መጠን 600 ከነበረበት ወደ 2ሺህ ከፍ አድርጓል፤ 35 በመቶ የግብር ክፍያ መጠን መነሻው ከ14 ሺህ ብር በላይ በሆነ ደሞዝ ላይ ይተገበራል።

ከገቢ ግብር ነፃ የተደረገው 2ሺህ ብር አጠቃላይ ከሀገሪቱ ገቢ 38 ነጥብ 44 ቢልዮን ብር እንደሚያሳጣ ተገልጿል።

የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ደሳለኝ ወዳጆ ፤ ማሻሸያ አዋጁ የሀገሪቱን የገቢ መሰብሰብ አቅም ለማሳደግ የተቀመጠውን ግብ ታሳቢ በማድረግና ለልማት ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተዘጋጀ መሆኑን ገልፀዋል።

ክልሉን ከአፈር ማዳበሪያ እዳ ነፃ ለማድረግ የክልሉ መንግስት የወሰደው እርምጃ የሚደነቅ መሆኑን በኢፌዴሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ገለፀ።

ክልሉን ከአፈር ማዳበሪያ እዳ ነፃ ለማድረግ የክልሉ መንግስት የወሰደው እርምጃ የሚደነቅ መሆኑን በኢፌዴሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ገለፀ።

(ሆሳዕና ፣ሐምሌ 10/2017) ፣የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ እና የግብርና ሚኒስቴር በቅንጅት በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የ2017/18 ምርት ዘመን የግብርና ግብዓት አቅርቦት እና ስርጭት ላይ የተደረገ ሱፐርቪዥን ግብረ መልስ ለክልሉ ግብርና ቢሮ ሰጥቷል።

በኢፌዴሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርናና ገጠር ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢና የቡድኑ መሪ የተከበሩ ሰለሞን ላሌ ብልሹ አሰራርን በመታገል ክልሉን ከአፈር ማዳበሪያ እዳ ነፃ ለማድረግ የክልሉ መንግስት የወሰደው እርምጃ የሚደነቅ መሆኑን ተናግረዋል።

በክልሉ የአፈር ማዳበሪያ አቅርቦትና ምርጥ ዘር ስርጭት ላይ መሻሻሎች መኖሩን ተናግረው እርሶ አደሩ አማራጭ የተፈጥሮ ማዳበሪያ በስፋት እንዲጠቀም መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል።

መንግስት ለዘላቂ ሰላም እና ለሀገራዊ አንድነት በትኩረት እየሰራ ይገኛል-ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር)

መንግስት ለዘላቂ ሰላም እና ለሀገራዊ አንድነት በትኩረት እየሰራ  ይገኛል-ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ሐምሌ 10/2017፦መንግስት ለዘላቂ ሰላም እና ለሀገራዊ አንድነት በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ እና ለዚህም አስተማማኝ መሰረት መጣሉን የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) ገለጹ።

የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) ለኢዜአ አመራሮች እና ሰራተኞች በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ እና ቀጣይ የስራ አቅጣጫ ሰጥተዋል።

ሚኒስትሩ በማብራሪያቸው፥ የተረጋጋ የፖለቲካ ስርዓት መሰረት የመጣል፣ገለልተኛ ተቋማትን የመገንባት እና ለሌብነት የማይመች የፖለቲካ ስርዓት መፍጠር ላይ ውጤታማ ስራዎች መከናወናቸውን አመልክተዋል።

ሚኒስትሩ አክለውም መንግስት ለዘላቂ ሰላም እና ለሀገራዊ አንድነት በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸው፥ ለዚህም አስተማማኝ መሰረት መጣሉን ተናግረዋል።

በክረምት ወራት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የሴቶችና ህፃናትን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትብብር መስራት እንደሚገባ ተመላከተ

በክረምት ወራት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የሴቶችና ህፃናትን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትብብር መስራት እንደሚገባ ተመላከተ

(ሆሳዕና፣ ሀምሌ 10/2017)፤ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ቢሮ እና የክልሉ የሴቶች አደረጃጀት የጋራ ፎረም የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ማስጀመሪያ መርሃ ግብር በማረቆ ልዩ ወረዳ አካሂደዋል።

በመርሃ ግብሩ የችግኝ ተከላ በቆሼ አጠቃላይ 2ተኛ ደረጃ ት/ቤት፣ የአቅመ ደካማ ቤት ግንባታ ማስጀመሪያ በኢላላ ጅረኖ ቀበሌና ለቀበሌው የሴቶች የልማት ህብረት ድጋፍ የተበረከተ ሲሆን፣ የሴቶችን የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሰሩ የሚገኙ የልማት ስራዎች የመስክ ምልከታም ተደርጓል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሴቶችና ህፃናት ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ዘቢባ መሐመድናስር፣ በክረምት ወራት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የሴቶችና ህፃናትን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትብብር መስራት ይገባል ብለዋል።

የክልሉ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ የሰላም ተምሳሌትነትን በዘላቂነት ለማረጋገጥ በቅንጅት የተሰራው ስራ አበራታች መሆኑን የክልሉ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የህግና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አስታወቀ

የክልሉ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ የሰላም ተምሳሌትነትን በዘላቂነት ለማረጋገጥ በቅንጅት የተሰራው ስራ አበራታች መሆኑን የክልሉ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የህግና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አስታወቀ

(ሆሳዕና፦ ሀምሌ 10/2017) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ቸወካዮች ምክር ቤት የህግና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሰላምና ፀጥታ 2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምን ገምግሟል።

የክልሉ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የህግና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ   ወ/ሮ መሰረት ወ/ሰንበት እንደገለፁት ቢሮው የሰላም  ተምሳሌትነትን በዘላቂነት ለማረጋገጥ በቅንጅት የተሰራው ስራ አበራታች  መሆኑን ገልፀዋል።

ቢሮው የክልሉን የሰላምና ፀጥታ ለማረጋገጥ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በተሰሩ ስራዎች ተጨባጭ ለውጦችን ለማስመዝገብ ተችሏል ነው ያሉት።